የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በክልሉ ጠንካራ ሕብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ቁሊቶ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠንካራ የሕብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡

በሀላባ ዞን "የተዋሃዱ ህብረት ስራ ዩኒየኖች ለሁለንተናዊ ብልፅግና "በሚል መሪ ሀሳብ የዩኒየኖች የውህደት መድረክ ተካሂዷል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑስማን ስሩር በወቅቱ እንዳሉት መንግስት የህብረት ስራ ማህበራት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል የሪፎርም ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡

የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት የሚጠበቅባቸውን ውጤት ከማስመዝገብ አኳያ በርካታ ጉድለቶች ያለባቸው መሆኑን ተከትሎ በአዲስ መልክ ሪፎርም ማድረግ ማስፈለጉንም ጠቁመዋል፡

ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ፣ በግብይት ስርዓት ውስጥ የሚስተዋለውን ችግር በመፍታትና የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡

በክልሉ ጠንካራ የህብረት ስራ ማህበራትን በማደራጀት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይም የክልሉ ህብረት ስራ ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ተመስገን ጎዴቦን ጨምሮ የዞኑ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የህብረት ስራ ማህበራት አመራሮች እየተሳተፉ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.