የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ መረባረብ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ የካቲት 19/2017 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ የግብርና ልማት ተግዳሮቶችን በመፍታት ምርታማነትን ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።

"የግብርና ምርታማነት ለብልፅግናችን" በሚል መሪ ቃል የክልሉ የ2017 ዓ.ም የበልግ አዝመራ ተግባራት ማስጀመሪያ ንቅናቄ መድረክ ዛሬ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ እየተካሄደ ነው።


ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እንዳሉት ባለፉት ዓመታት በክልሉ ምርታማነትን ለማሳደግ በተደረገ ጥረት ውጤት ተመዝግቧል።

ይሁንና የአየር ንብረት ለውጥ፣ የተባይና የአረም ቁጥጥር፣ የቴክኖሎጂ አጠቀቀም ውስንነት እንዲሁም የድህረ ምርት አያያዝና የገበያ ትስስር በክልሉ የግብርና ልማት ፈተናዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።

እነዚህን የግብርና ልማት ተግዳሮቶች በመፍታት የበልግ እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ባለድርሻ አካላት በርብርብ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ለመውጣት በሚደረገው ጥረት በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ የልማት አርበኛ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በምክትል ርእሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው ክልሉ በሀገር ደረጃ ያለውን የምርት ድርሻ ለማሳደግ ለበልግ አዝመራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።

በተለይ የሜካናይዝድ እና የኩታ ገጠም እርሻ ልማትን ከማጠናከር ባለፈ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

በዚህም በተያዘው የበልግ እርሻ በክልሉ ከ848 ሺህ 155 ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከ77 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።

ለዕቅዱ ስኬታማነት የምርምር ተቋማት፣ የግብርና ሴክተርና ባለድርሻ አካት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ቢሮ ሀላፊው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026