
አዲስ አበባ ፤የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር ሊገባ እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የዘርፎች አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አፈፃፀም በመጀመሪያ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሪፎርሙ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር ለመቀየር የተደረገው ጥረት አበረታች
ነው፡፡
በዘርፉ የሚሰጠው ስልጠና የሥራ ገበያውን ፍላጎት የሚመልስ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
የስልጠናውን ጥራትና አግባብነት ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ ነው ያሉት ሚኒስትሯ የሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓቱን ለማሻሻል የተጀመረው ሥራ በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
በገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ግብዓትና ግብይት ላይ ያተኮረ የሙያ ደረጃና ስርዓተ ስልጠና ዝግጅት፣ ተቋማትን በአንፃራዊ የመልማት ፀጋ ለማደራጀት የተጀመረውን ሥራ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር፣ የማሰልጠኛ ተቋማት ኢንተርፕራይዝ ሥራ የገበያ ክፍተቱን በሚሞላ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሚፈለገው ደረጃና ጥራት እንዲያከናውኑ ድጋፍና ክትትል ማድረግ የዘርፉ የቀጣይ ወራት ትኩረት እንደሆኑ መገለፁን ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026