የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በምስራቅ ጎጃም ዞን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል - አስተዳደሩ</p>

Feb 25, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤ የካቲት 17/2017(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የዞኑ መስተዳድር አስታወቀ።

የዞኑ መስተዳደር ባለፉት ሰባት ወራት የተከናወኑ ተግባራትን በደብረማርቆስ ከተማ ገምግሟል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ በወቅቱ እንዳሉት በወረዳና በቀበሌዎች በርካታ ህዝባዊ መድረኮችን በማዘጋጀት ከማህበረሰቡ ጋር በመምከር ሰላምን የሚያጸኑ ተግባራት ተከናውነዋል ።

በዚህም ከ51ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ብለዋል።

በተለይም በትምህርት፣ በጤና፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በስራ እድል ፈጠራ ዘርፎች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

የተማሪዎችን መጠነ ማቋረጥ መቀነስ እንዲሁም የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚዎችን ቁጥር ማሳደግ መቻሉን አመልክተዋል።

ህብረተሰቡን በማሳተፍ የሚከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል ።

የዞኑ የትምህርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ በበኩላቸው የተገኘው ሰላም በማህበራዊ ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን ተቀናጅተን ለመፍታት አስችሎናል ብለዋል።

አሁን ላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን መውሰድ የሚያስችል ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የማህበረሰቡን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ የተሰራው ስራ አበረታች ለውጥ አምጥቷል ያሉት ደግሞ የዞኑ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ አበባው በለጠ ናቸው።

ህብረተሰቡን በማስተባበር የመጣውን ለውጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ አመላክተዋል።

በግምገማ መድረኩ የዞኑ መስሪያ ቤቶች ሃላፊዎችና ባለድርሻ አካላትተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.