የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ፕሮግራሙ እራሳችንን በመቻል ጥሪት እንድናፈራ አግዞናል -ተጠቃሚዎች</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር ፤ጥር 3/2017 (ኢዜአ) ፡- በደብረብርሃን ከተማ ሲካሄድ በቆየው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም በገቢ ማስገኛ ሥራዎች እራሳቸውን በመቻል ጥሪት እንዲያፈሩ ያገዛቸው መሆኑን በከተማው የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ተናገሩ።

በከተማው የመጀመሪያው ዙር የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው ጥሪት ያፈሩ 442 የቤተሰብ ሀላፊዎች ዛሬ ተመርቀዋል።

ፕሮግራሙ የምግብ ክፍተት በመሙላት የቤተሰብና የወል ጥሪት መገንባት ላይ ዓላማ አድርጎ የተነሳ ነው ፡፡

ትኩረቱም በተፈጥሮ ችግር ምክንያት የምርት መቀነስ የሚታይባቸው አካባቢዎች የሚኖሩና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለጉዳት እንዳይጋለጡ መደገፍ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ይህን መሰረት አድርጎ በፕሮግራሙ የታቀፉ ወገኖች የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ አልፈው ሀብት በማፍራት ዛሬ በደብረብርሃን የተመረቁት ማሳያ ናቸው።

ተመራቂዎቹ በከተማ ግብርና፣በአገልግሎት፣ በንግድና በማንፋክቸሪንግ ዘርፎች በመሰማራት ከራሳቸው አልፎ ለአካባቢያቸው ወጣቶች የስራ እድል ፈጥረዋል።

ከፕሮግራሙ ተመራቂዎች መካከል አቶ አርጋው ገብሩ ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ባገኙት ሥልጠናና የገንዘብ ድጋፍ የተሻሻሉ የወተት ላሞች በማርባት በቀን በአማካይ 17 ሊትር ወተት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከወተት ሽያጩ የሚያገኙት ገቢ ከእለት ፍጆታቸው አልፈው ከ500 ሺህ ብር በላይ መቆጠባቸውን አስረድተዋል።

ሌላኛዋ የፕሮግራሙ ተመራቂ ወይዘሮ ትግስት በቀለ በበኩላቸው፤ በከተማ ምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው ጠንክረው በመስራት ኑሯቸውን መለወጣቸውን ገልጸዋል።


የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በወቅቱ እንደገለጹት፤ በከተማ ሲካሄድ የቆየው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም የስራ ባህልን በማሻሻል በማህበረሰቡ ዘንድ የቁጠባ ባህል እንዲጎለብት አግዟል።

ጥሪት አፍርተው ከፕሮግራሙ የተመርቁት ወገኖች በቀጣይ በሚሰማሩበት አዋጭ የስራ ዘርፍ በዘላቂነት ውጤታማ ሆነው እንዲቀጥሉ የአስተዳደሩ ድጋፍ እንደማይለያቸው ተናግረዋል።

የአስተዳደሩ ምግብ ዋስትናና ሴፍትኔት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ግርማ ዲባቤ፤ ተመራቂዎቹ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሰርተው ራሳቸውን በመቻል ጥሪት ያፈሩ 442 የቤተሰብ ሀላፊዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.