የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ባለፉት ስድስት ወራት ከቡና የወጪ ንግድ 908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኘ</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ204 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለወጪ ገበያ በመላክ ከ908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ዑመር ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ ከቡና ውጪ ንግድ 2 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።

በዚህም ወደ ውጭ ከተላከው ከ204 ሺህ 206 ቶን ቡና ውስጥ ባለፉት ስድስት ወራት 908 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኙቱን ተናግረዋል።

ይህም በዕቅዱ አንጻር 127 በመቶ ብልጫ ያለው ገቢ መሆኑን ጠቁመው፤ አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ከተገኘው 571 ሚሊየን ጋር ሲነጻጻር ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ ወራትም የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.