የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በክልሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው ቀጥለዋል- አቶ ኦርዲን በድሪ</p>

Jan 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተመልክተዋል።

አቶ ኦርዲን በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኮሪደር ልማት ስራው በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።


በተለይም በከተማው በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የአባድር ፕላዛ በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ከግንባታው ስራ ጎን ለጎን እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

የአባድር ፕላዛ አካባቢውን ባማከለ መልኩ ከዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ ጋር በማስተሳሰር እየተከናወነ እንደሚገኝና የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር በማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።


በቀጣይም በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው አመራሩ የራሱን ሚና ሊጫወት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ ማሳሰባቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.