የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በክልሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው ቀጥለዋል- አቶ ኦርዲን በድሪ</p>

Jan 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተመልክተዋል።

አቶ ኦርዲን በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኮሪደር ልማት ስራው በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።


በተለይም በከተማው በ1 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የአባድር ፕላዛ በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ከግንባታው ስራ ጎን ለጎን እየተከናወኑ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

የአባድር ፕላዛ አካባቢውን ባማከለ መልኩ ከዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ ጋር በማስተሳሰር እየተከናወነ እንደሚገኝና የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር በማድረግ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።


በቀጣይም በክልሉ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው አመራሩ የራሱን ሚና ሊጫወት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ ማሳሰባቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026