የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዩኒቨርሲቲው የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያፋጥኑ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን አጠናክሮ ይቀጥላል

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጉዞ የሚያፋጥኑ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

"ትምህርትን በምርምር፣ በዲጂታላይዜሽን፣ በፈጠራና በኢንዱስትሪ ትብብር ማሳደግ" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀው የምርምር፣ የፈጠራና የአውደ-ርዕይ ሳምንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ ተጀምሯል፡፡


ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በሚቆየው በዚህ አውደ-ርዕይ ላይ ሳይንሳዊ የፓናል ውይይቶች የሚካሄዱ ሲሆን፣ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ግኝቶች ለጉብኝት ቀርበዋል።

የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በመክፈቻው ላይ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ያለውን ሰፊ ተሞክሮ በመጠቀም ለሀገር ግንባታ የሚሰጠውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል።

በትምህርት ዘርፉ የሚከናወኑ ማናቸውም ተግባራት የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያፋጥኑ መሆን እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ምርምሮቻችን የሕዝባችንን ችግር ሊፈቱ ይገባል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ዩኒቨርሲቲው የሚያመነጫቸው እውቀቶችና የፈጠራ ሃሳቦች ወደ ተግባራዊ መፍትሄ እንዲቀየሩ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በዩኒቨርሲቲውና በኢንዱስትሪው መካከል ያለውን ቅንጅት በማጠናከር፣ የምርምር ውጤቶች በቀጥታ ለኢንዱስትሪው ግብዓት የሚሆኑበት ሥርዓት መዘርጋቱንም አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዲን የቆየአለም ደሴ (ዶ/ር)፤ አውደ-ርዕዩ በዋናነት በትምህርት፣ በምርምር፣ በዲጂታላይዜሽንና በኢንዱስትሪ ትብብር ላይ ያተኮረ መሆኑን አመልክተዋል።


የኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ያለውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን አዳዲስ ግኝቶች ወሳኝ ሚና እንዳላቸው የገለጹት ዲኑ፤ ትምህርት በዲጂታል አማራጮች ተደግፎ ለሁሉም ዜጋ ተደራሽ እንዲሆን መስራት ዋነኛ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ትምህርት ከንድፈ-ሃሳብ ባለፈ የተማሪዎችንና የተመራማሪዎችን አቅም ወደ ተግባር የሚለውጥ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ይህ አውደ-ርዕይ በምሁራን፣ በተማሪዎችና በባለድርሻ አካላት መካከል ጠንካራ የልምድ ልውውጥ የሚደረግበትና የወደፊት የትብብር መድረክ የሚፈጠርበት ታላቅ አጋጣሚ እንደሚሆን ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026