የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ቁልፍ ሚና ይጫወታል

Apr 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 14/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ዜጎች የመንግሥትን አገልግሎት በቅርበት እንዲያገኙ በማድረግ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎትን አስጀምረዋል።

በዚሁ ወቅት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ለመንግሥት አገልግሎት መሳለጥ ወሳኝ መሰረት ጥሏል ብለዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂም በቅርቡ ወደ ስራ በማስገባት የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እያሳለጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


በኢትዮጵያ ከዓመታት በፊት የሚሰጡ የመንግሥት አገልግሎቶች የዜጎች እንግልት ምንጭ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ለዚህም ከዓመት ወዲህ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስጀመር ዜጎች የመንግሥት አገልግሎቶችን ፈጣን፣ ዘመናዊና ግልፅ በሆነ አሰራር እንዲያገኙ እያስቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

የዲጂታል እመርታ መንግሥት የአገልግሎት ቅልጥፍና መገለጫ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም ዜጎች በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።

ይህም እንግልትን በማስቀረት የመንግሥትን የሥራ ሂደት በማፋጠን የተሻለ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስረድተዋል።

ለአብነትም የዲጂታል መታወቂያን ጨምሮ የተበታተኑ የመንግሥት አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል መሰጠት ሲችሉ ከፍተኛ ሀገራዊ ፋይዳ እንዳላቸው አብራርተዋል።


በአዲስ አበባ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሎች ጭምር የተደራሽነት አድማሱን በማስፋት ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል።

በቀጣይም በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዕቅድ መነሻነት የተገኘውን እመርታ በማስፋት የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አቅም ለመገንባት መትጋት ይጠይቃል ብለዋል።

የአዲስ አበባ መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መንግሥት አገልግሎቶችን ወደ ዜጎቹ ለማቅረብ ታስቦ ሥራ ላይ የዋለ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም ገልጸዋል።

ይህም ዜጎች ባሉበት ቦታ የሚቀርብላቸውን የመንግሥት አገልግሎቶች በጥራት እንዲያገኙ በማስቻል ዲጂታል ኢኮኖሚና ሀገር ለመገንባት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026