የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዘመናዊ አሰራሮችን በመተግበር በሀገር ግንባታ ሂደት የበኩሉን እየተወጣ ነው

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዘመናዊ አሰራሮችን በመተግበር በሀገር ግንባታ ሂደት የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) አመለከቱ፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የ75ኛ ዓመት የአልማዝ እዮቤልዩ በዓል መክፈቻ ሥነ ሥርዓት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተካሂዷል።


አስተዳደሩ ከምስረታው ጀምሮ አሁን የደረሰበትን ልህቀት ስኬቶችና ተሞክሮዎችን የሚያስቃኝ አውደ ርዕይም በማዕከሉ ተከፍቷል።

የተለያዩ ከያኒያንም በዓሉን በማስመልከት ልዩ ልዩ የኪነ ጥበብ ሥራዎችን አቅርበዋል።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አስተዳደሩ በሀገር ግንባታ ሂደት በአርዓያነት የሚጠቀስ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

በተቋም ግንባታ በኩልም አስተዳደሩ ምሳሌ የሚሆን ተግባራትን አከናውኗል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ለዘርፉ ዕድገት ጠንካራ የግል ተቋራጭና አማካሪዎች እንዲፈጠሩ የማይተካ ሚና መጫወቱን ተናግረዋል።


የዘርፉን ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ባለሙያዎችም እንዲበቁ በማድረግ ረገድ ተቋሙ ያከናወናቸው ተግባራትም በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገር የመገንባት ሂደቱን ውጤታማ በሆነ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ አስችሏል ብለዋል።

አስተዳደሩ በቀጣይም ዘመኑን የዋጁ አሰራሮች በመከተልና ጥናትና ምርምሮችን መሰረት በማድረግ ለላቀ ውጤት ሊተጋ እንደሚገባም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በበኩላቸው፤ አስተዳደሩ ዘመኑን የዋጁ አሰራሮችን በመከተል ብልፅግናን የሚያረጋግጡ ወጤታማ ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ለውጤት የበቁ ዘመናዊ የፍጥነት መንገዶች፣ የተለያዩ ድልድዮች እንዲሁም ተቋሙ የተከተላቸው የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀሞች ለስኬቱ ማሳያዎች ናቸው ብለዋል።

የአልማዝ እዮቤልዩ በዓሉ የተሻለች እና ዘመናዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት ቃላችንን የምናድስበት ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የምህንድስናን ጥበብ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

አስተዳደሩ ጥናትና ምርምርን ማዕከል ያደረጉ ሥራዎችንም በሰፊው ገቢራዊ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026