የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ሀገር አቀፍ ጥናቱ ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት መሰረት ይጥላል

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ሚያዝያ 12/2018(ኢዜአ)፦የመንግስት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ ሀገር አቀፍ ጥናት ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ለመገንባት መሰረት እንደሚጥል የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ገለፀ።

ለድሬዳዋ አስተዳደርና ለሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች የመንግሥት ሠራተኞች የፐርሶኔል መረጃ ማጥራትና ማረጋገጥ ጥናቱን ለመተግበር የሚያስችላቸው ስልጠና ዛሬ ተሰጥቷል።


በስልጠናው ላይ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ግርማ ፤ እንደ ሀገር የሚካሄደው የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ ጥናት የሰው ኃይል ስራ አመራርን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ጥናቱ ትክክለኛ መረጃን በማረጋገጥና የተቋማትን የመረጃ አያያዝ ክፍተት በመሙላት የሰው ሃብት የመረጃ አያያዝን ዲጂታላይዝ ማድረግ እንደሚያስችል ጠቁመዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ጥናቱ ወደ ዘመናዊ እና አውቶሜትድ የሰው ሃይል ስራ አመራር ስርአት ለመሸጋገር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ነው አቶ ሙሉጌታ የገለፁት።

ለጥናቱ መሳካት አስፈላጊው ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ ወር መጨረሻ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት ጥናቱ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር የሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሰቦ አህመድ በበኩላቸው፤ ሀገር አቀፉ ጥናት ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር የህዝብን መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በላቀ ተጠያቂነት እና ግልፀኝነት ለመፈፀም ቁልፍ አበርክቶ እንዳለው አንስተዋል።


በሚሰበሰበው ትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ሠራተኞች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች መንግስት በፍጥነት ምላሽ ለመስጠትና ሠራተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል።

በተጨማሪም ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን በማስወገድ ከሰው ንክኪ የፀዱ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የመንግስትና የህዝብ ሃብት ከብክነት ለመከላከል ሚናው የጎላ መሆኑን አስታውቀዋል።

ጥናቱ እንደ ሀገር የተጀመሩትን ውጤታማ የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጦችን በማላቅ የብልጽግና ጉዞን ይበልጥ ለማፋጠን ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው የገለፁት ደግሞ የሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ አብዱረህማን ናቸው።


አቶ መሐመድ አክለውም፤ ለጥናቱ መሳካት የተመደቡ አስተባባሪዎች ፣ የተቋማት የሰው ሃብት ስራ አመራር ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች በላቀ ቁርጠኝነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026