የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ያላትን ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አጋራች

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘርፍ ያካበተችውን ተጨባጭ ልምድ ለአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አባላት አጋርታለች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የመሩትን የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሚኒስትሮች ስብሰባን አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት የሊቀ መንበርነት ሚናዋን በብቃት እየተወጣች መሆኑን ገልጸዋል።


ዛሬ በበይነ-መረብ በተካሄደው በዚህ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለማጋራት አመቺ ዕድል መፈጠሩን ቃል አቀባዩ አንስተዋል።

ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለኢኮኖሚ፣ ለአስተዳደር እንዲሁም ለሰላምና ፀጥታ ሥራ ያለውን የጎላ ፋይዳ ለሚኒስትሮቹ አስገንዝበዋል ብለዋል።

በተለይም ቴክኖሎጂው ግጭቶችን በመከላከል፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን በማስተላለፍ እና የሰላም ሂደቶችን በመደገፍ ረገድ ያለውን አበርክቶ አብራርተዋል።

አምባሳደር ነብያት አክለውም፣ በአሁኑ ወቅት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቅንጦት ሳይሆን ጠቃሚ የልማት መሣሪያ መሆኑን ኢትዮጵያ ተገንዝባለች ብለዋል።

በዚህ ዘርፍም የተቀናጁ ተቋማትን በማቋቋም ህዝቡ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም ቀልጣፋ ዲጂታል አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተሞክሮ እና በአቅም ግንባታ ረገድ እየተከናወነ ያለውን የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ በአብነት ለመድረኩ መቅረቡን ተናግረዋል።

በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ሻምፒዮን ሆነው መመረጣቸው፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ተሞክሮ ለሌሎች ሀገራት እንድታካፍል ትልቅ ዕድል መፍጠሩን አምባሳደሩ ገልጸዋል።

አፍሪካ በቀደመው የኢንተርኔት ዘመን ዘግይታ መግባቷን ያስታወሱት ቃል አቀባዩ፤ አሁን ግን አህጉሪቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ዘመን ተገቢውን ቦታ በመያዝ የመሪነት ሚና እንዲኖራት ኢትዮጵያ ያላትን ጽኑ አቋም በመድረኩ ማንጸባረቋን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026