የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሴቶችን የንግድ ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018 (ኢዜአ)፡-ሴቶች በንግድ ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት በተጠናከረ መንገድ እየተከናወኑ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

በሥርዓተ ጾታ እኩልነትና የሴቶች ተጠቃሚነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው 15ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴክሬታሪያት የቴክኒካል ኮሚቴ አህጉራዊ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ኸይረዲን በዚህ ወቅት፤ኢትዮጵያ የገጠርና የከተማ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልዩ ልዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች ብለዋል።

የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስትራቴጂ ተቀርፆ ወደ ተግባር መገባቱን አውስተው፤በዚህም በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣በስራ እድል ፈጠራና በሌሎች ዘርፎች ላይ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰዋል።


የአፍሪካውያን ሴቶችን በንግድ ስርዓቱ ላይ ተሳታፊና እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡

ሴቶች በንግድ ላይ ለመሳተፍ ማነቆ የሆኑባቸውን ተግዳሮት በመፍታት ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የኮሜሳ አባል ሀገራት ተቀራርበን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

የዛሬው ምክክርም ይህን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ውይይቱ አፍሪካውያን ሴቶች በንግድ ስርዓቱ ላይ ያላቸውን ተጠቃሚነት ማሳደግ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ወደ ተግባር መቀየር የሚቻልበትን እድል የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል።

የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) ረዳት ፀሀፊ አምባሳደር ማህመድ ካዳ በበኩላቸው፤ኢትዮጵያ የሥርዓተ ፆታ እኩልነትንና የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማስፈን ለምታሳየው የአመራር ቁርጠኝነት አመሰግነዋል።


እንደ አህጉር የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚሰሩ ስራዎች አበረታች ቢሆንም ቀሪ ስራዎች መኖራቸውንአንስተዋል።

በተለይም በአፍሪካ ሴቶች የፋይናንስ፣የዲጂታል ክህሎት፣ የገበያ፣ የውሳኔ ሰጪነት ያላቸውን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንፃር ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል።

15ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴክሪቴሪያት ቴክኒካል ኮሚቴ አህጉራዊ ስብሰባ እነዚህን ክፍተቶች ለመሙላት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026