የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኦሮሚያ ክልል ለትንሳኤ በዓል ፍጆታ የሚውሉ መሰረታዊ ምርቶች በተሻለ ሁኔታ እንዲቀርቡ እየተሰራ ነው

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ለዘንድሮ የትንሳኤ በዓል ፍጆታ የሚውሉ መሰረታዊ ምርቶች በተሻለ ሁኔታ ለገበያ እንዲቀርቡ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ንግድ ቢሮ የገበያ ልማት ዳይሬክተር አቶ ጉቱ ተመስጌን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ለዘንድሮው የትንሳኤ በዓል የተሻለ የምርት አቅርቦት እንዲኖርና ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ ከባለድርሻ አካላት ጋር እቅድ በማውጣት የተለያዩ ተግባራት እየተሰሩ ነው።

በክልሉ በቂ ምርት ያለበት አከባቢና የዋጋ ሁኔታን በማጥናት ወደ ሌሎች የምርት አቅርቦት እጥረት ያለበት ቦታዎች እንዲደርስና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በተለይም አትክልትና ፍራፍሬ፣የቁም እንስሳት፣ እንቁላልና ዶሮ እንዲሁም ሌሎች በስፋት የሚቀርቡ የበዓል ፍጆታዎች መሆናቸውን ገልጸው፤ ዘይትና ስኳር ደግሞ በማህበራትና ዩኒየኖች በኩል እንዲቀርቡ ተደርገዋል ብለዋል።

ምርቶቹም በክልሉ ባሉት 775 የሰንበት ገበያዎችና በዐውደ ርዕይና ባዛሮች ላይ እየቀረቡ እንዳሉ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣በተለይም ሁለት ቀናት ብቻ የነበረው የሰንበት ገበያ ለበዓሉ ለ10 ተከታታይ ቃናት እንዲከፈት ተደርጓል ብለዋል።

ለበዓል ፍጆታ የሚውሉ በቂ መሰረታዊ ምርት እንዳለ የተናገሩት አቶ ጉቱ፣ አቅርቦቱን ለማሳለጥና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር የክትትልና ቁጥጥር ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026