🔇Unmute
ሐረር፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የነዳጅ አቅርቦቱ በቁጠባና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን መሰረት ባደረጉ መልኩ እየተሰራጨ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር ገለጹ።
በክልሉ የሚቀርበውን ነዳጅ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተጠናከረ መልኩ ተግባራዊ በሚደረግበት ሁኔታ ላይ በክልሉ የተቋቋመው ስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት አድርጓል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ሮዛ ኡመር፤ በውይይት መድረኩ ላይ እንዳሉት በክልሉ የነዳጅ ስርጭትና አጠቃቀሙ በተቀመጠው የመፍትሄ አቅጣጫ መሰረት ይቀጥላል ብለዋል።
ለዚህም ኮሚቴው በትኩረት መስራት እንዳለበት አስገንዝበው የሚቀርበው ነዳጅ በቁጠባና ትኩረትን የሚሹ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን መሰረት አድርጎ መሆን እንዳለበት አጽኖት ሰጥተዋል።
በክልሉ የተቋቋመው ግብረ ሃይል የክትትልና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበው፤ በህገ ወጥ ተግባር ላይ የሚሳተፉ ካሉ የተጠናከረ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ያልተገባ የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ በሚያደርጉ አሽከርካሪዎችና ከነዳጅ ጋር ተያያዥነት ሳይኖራቸው በሸቀጦችና በምርቶች የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ በተመሳሳይ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።
በመንግስት ተቋማት የሚገኙ ተሽከርካሪዎች ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀሙ የማድረግና በነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚከናወኑ የነዳጅ ግብይቶች የቁጥጥር ሰራ እየተተገበረ መሆኑንም ተናግረዋል።
በምድረኩ የተገኙት የግብረ ሃይል አባላቱ በመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ሁኔታ በነዳጅ አቅርቦት ላይ የፈጠረውን ችግር ለመቋቋም የተቀመጡ የመፍትሄ አቅጣጫዎችንና እየተከናወኑ የሚገኙ አሰራሮችን በአግባቡ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን የመፍትሄ አቅጣጫዎች በተመለከተ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል።
በተለይም ነዳጅን በቁጠባ መጠቀም፣ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን የመጠቀም ልምድ፣ የእግር ጉዞ ባህልን ማጎልበት፣ የሕዝብ ትራንስፖርትን መጠቀም፣ በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ማጋለጥ እና ሌሎችም ከህብረተሰቡ የሚጠበቁ ዋና ዋና ተግባራት መሆናቸውን አፅኖት ሰጥተዋል።
ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
May 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026