የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በገጠር ኮሪደር ልማት ከጨለማ ወደ ብርሃን በመሸጋገር አዲስ የህይወት ምእራፍ ጀምረናል- አርሶ አደሮች

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀላባ ፤መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- በገጠር ኮሪደር ልማት ከጨለማ ወደ ብርሃን በመሸጋገር አዲስ የህይወት ምእራፍ በመጀመራችን ተደስተናል ሲሉ በሀላባ ዞን የሲምቢጣ ቀበሌ አርሶ አደሮች ተናገሩ።

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ የሲምቢጣ ቀበሌ ነዋሪዎች በምሽት የብርሃን አድማስ ታጅበው መኖር ከጀመሩ ወራቶች እየተቆጠሩ ነው።


በድቅድቅ ጨለማ ህይወታቸውን ይመሩ የነበሩ አርሶ አደሮች አሁን ላይ ምሽቱን በብርሃን የሚረማመዱበት መንደር ሆኖላቸዋል።

በቀበሌው የሚኖሩት አርሶ አደር ገረመው መሀመድ እና ባለቤታቸው አሁን ላይ መሽቶ በጨለማ እንቸገራለን የሚል ስጋት የለም፤ “የጨለማ ህይወትም አብቅቷል” ይላሉ።

ልጆቻቸው ያለምንም ስጋት በምሽትም ይሁን በሌሊት መብራት አብርተው ማጥናት የቻሉበት፤ ተንቀሳቃሽ የእጅ ስልክ ያለ ሃይል እጦት መጠቀም የቻሉበት አጋጣሚ በመፈጠሩ መደሰታቸውን ይናገራሉ።

ለእኛም ለልጆቻችንም አዲስ ህይወት መኖር ጀምረናል የሚሉት አርሶ አደር ገረመው፤ የአኗኗር ዘይቤያቸው አሁን ላይ በመሰረታዊነት የተለወጠ በመሆኑ በጨለማ የኖርነው ህይወት የሚያስቆጭ ነው ይላሉ።


በቀበሌው የሚኖሩት አርሶ አደር ሎባ ባላ እና ወይዘሮ ፈዲላ አወል፤ ከጨለማ ህይወት ወጥተን በአዲስ ምእራፍ አዲስ ህይወት መኖር በመጀመራችን ተደስተናል ብለዋል።

በጓሯችን አትክልት፣ ፍራፍሬና አዝመራው፤ በቤታችን መብራቱ ተመቻችቶልን የመኖር እድል በማግኘታችን እኛም ይሁን ቤተሰባችን ደስተኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።


የከበደው የኑሮ ዘይቤ አሁን ላይ ምቹ እና ቀላል በመሆኑ ደስተኞች ነን ያሉት ነዋሪዎቹ በብርሃን የታጀበ አዲስ የህይወት ምእራፍ መኖር የጀመርን በመሆኑ ለዚህ ስኬት ላበቁን የመንግስት አካላት እናመሰግናለን ብለዋል።


የሲምቢጣ ቀበሌ ነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ ከጨለማ ወደ ብርሃን ብሎም ወደ ዘመናዊ አኗኗር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጭነት በተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት ነው።

በዚህ የልማት ኢንሼቲቭ በማእከላዊ ኢትዮጵያ የተለያዩ ወረዳዎች ተከናውኖ የበርካታ አርሶ አደሮችን ህይወት መለወጥ ያስቻለ ሆኗል።


የልማት ስራውን በገጠሪቷ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በማዳረስ የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ በመለወጥ የተሻለ ህይወት መምራት እንዲችሉ እየተደረገ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026