የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመግታት ቅንጅታዊ አሰራሮች ይጠናከራሉ

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመግታት የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርአያስላሴ ገለጹ።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው እና የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበርን መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው።


"ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ስርዓት ለሀገር ዕድገት" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው አውደ ጥናት ላይ የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበር በኢትዮጵያ ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።

የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርአያስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ተግባራዊ በተደረገው የዲጂታል ፋይናንስ ስርዓት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች ተገኝተዋል።


ዲጂታል ስትራቴጂ 2025ን ጨምሮ በዲጂታል 2030 ለዲጂታል ፋይናንስ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ገልጸው ይህም ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት በሚደረገው ሀገራዊ ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም የዲጂታል ፋይናንስ ደህንነትን ለማስጠበቅና ከማጭበርበር ወንጀሎች ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህንንም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመከላከል ቅንጅታዊ አሰራሮች እንደሚጠናከሩ አመልክተው፤ የፍትህ አካላት፣ የጸጥታና ደህንነት ተቋማትን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው ብለዋል።


የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፤ አውደ ጥናቱ የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀለኞችን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራትን ለማቀናጀት ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

በአውደ ጥናቱ የጥናት ውጤቶችን መሰረት ያደረጉ የመፍትሔ ሃሳቦች ቀርበው በባለድርሻ አካላት ውይይት እንደሚደረግባቸውም ተናግረዋል።

የህግ ክፍተቶችን መለየትና የቁጥጥር ስራዎችን ማጠናከር ሌላው የአውደ ጥናቱ ዓላማ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026