የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአዲስ አበባ ፈጣን የልማት ዕድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን የሚያሳይ ነው

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስደናቂ የልማት ዕድገት የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።


በመርሃ ግብሩ ላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የጣሊያን የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ማሪያ ትሪፖዲ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ እና ተጋባዦች ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የመዲናዋ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ የልማት ስኬቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻነትን እያሳደገ ነው።

የዓለም ሶስተኛዋ የዲፕሎማሲ ማዕከል የአፍሪካ መዲናና ውቧ አዲስ አበባ የአህጉሪቷ የመግቢያ በርነትን በፍጥነት እያሳደገች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባን ምቹና ተወዳዳሪነት ለማሳለጥ በተገነቡ የመሰረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች ውስጥ የነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ቅድሚያ እንደተሰጠው አስረድተዋል።

በመዲናዋ በመሠረተ ልማት መስክ የተመዘገቡ ውጤቶችም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ትልም ፍሬ እያፈራ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የአገልግሎት አሰጣጠን ለማሳለጥ የተወሰዱ ርምጃዎች ኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት የስበት ማዕከል እያደረጋት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

የአዲስ አበባ የአዲስ መሶብ የዲጂታል የአንድ ማዕከል ለአልሚ ባለሃብቶች የተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት የሚያገኙበትን አስቻይ ምኅዳር መፍጠሩንም ገልጸዋል።

የአዲስ አበባን ፈጣን ዕድገት በማሳለጥ ምቹ የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ እያበረታታ መሆኑን አንስተዋል።

የመጀመሪያው የኢትዮ-ጣሊያን የኮንስትራክሽን፣ የመሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ፎረም የመዲናዋን የኢንቨስትመንት አማራጮች ለማሳየት ገንቢ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያና ጣሊያን ወዳጅነት በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ የሀገራቱ ታሪካዊ ወዳጅነትም የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብርን በማጠናከር ከፍተኛ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በንግድና ኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አልሚ ባለሃብቶች ድጋፍና ትብብር እንደሚደረግ ጠቅሰው፤ የጣሊያን ባለሃብቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026