የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በፌዴራልና በክልሎች መካከል ያለውን የጋራ ገቢ ክፍፍል ፍትሃዊ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤት አምጥተዋል-አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦በፌዴራልና በክልሎች መካከል ያለውን የጋራ ገቢ ክፍፍል ፍትሃዊ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤት ማምጣታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አስታወቁ።

ምክር ቤቱ በበይነ-መንግሥታት የፌዴራል ግንኙነትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።


የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በመድረኩ ላይ እንዳስታወቁት፤ የምክር ቤቱ አንዱና ዋነኛው ተግባር ፍትሃዊ ልማትና ዕድገት እንዲኖር ማስቻል ነው።

ለዚህም ተፈጻሚነት ባለፉት አምስት ዓመታት አዳዲስ አሠራሮችን የመዘርጋትና ነባሮቹን የማሻሻል ተግባራት ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል።

በተለይም በጋራ ገቢዎች ክፍፍል ቀመር ላይ የተደረገው መሠረታዊ ማሻሻያ የክልሎችን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ጠቁመዋል።

"ከማሻሻያው በፊት 4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረው የክልሎች የጋራ ገቢ ድርሻ፤ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ወደ 91 ነጥብ 73 ቢሊዮን ብር እንዲያድግ ተደርጓል" ብለዋል።

ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው የገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ዝውውርን የሚያፋጥን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት በመዘርጋቱና የምክር ቤቱን ውሳኔዎች በፍጥነት ወደ ተግባር በመቀየሩ መሆኑን አመልክተዋል።

ከዚህ ባለፈም ከከፍተኛ ማዕድን ሀብቶች የሚሰበሰበው የሮያሊቲ ገቢ ክፍፍልም መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል።

ምንም እንኳ አመርቂ ውጤቶች ቢመዘገቡም አሁንም ያልተሻገርናቸው ተግዳሮቶች መኖራቸውን ያነሱት አፈ ጉባኤው፣ በተለይም ከፌዴራል ተቋማት ወደ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚተላለፉ ድጎማዎች ላይ የአሳታፊነትና የግልጸኝነት ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።

ሥልጠናው እነዚህን ክፍተቶች ለመሙላት እንደሚያግዝም አስረድተዋል።


በምክር ቤቱ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ኃይሉ ኢፋ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ የዜጎችን ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የሕግ ማዕቀፎችንና ግልጽ የአሠራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የስልጠና መድረኩም በሀብት ክፍፍል ሥርዓቱ ላይ መተማመንን በመፍጠር ለፌዴራል ሥርዓቱ መጠናከር የጎላ ሚና እንደሚኖረው አስታውቀዋል።

በመድረኩ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025