የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ የካቲት 25/2018(ኢዜአ)፦ ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ዜጎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ እንደሚያስችል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ ተናገሩ።

ፋይዳ መታወቂያን ከተለያዩ አገልግሎቶች ጋር ማስተሳሰር ከተጀመረ ወዲህ የተመዝጋቢዎች ቁጥር እየጨመረ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ቀጣይ 5 ዓመታት የሚመራበትን ''ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ'' በቅርቡ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትግበራ በሁለንተናዊ ዘርፍ በተለይም የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ አጋዥ ሚና ይኖረዋል።

በዚህ ዙሪያ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ዓሊ እንዳሉት ዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ስርዓቱን ለማዘመን እያገዘ ነው።

ዘመኑ ያፈራውን የዲጂታል አሰራር እውን በማድረግ በቀላሉ መግባባት፣ መረጃዎችን መቀባበልና በተለይም የግብይትም ሆነ ሌሎች አገልግሎቶችን በፍጥነት ለማግኝት እንደሚረዳ ነው የገለጹት።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለማፋጠንና ከዘርፉም ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠቃሚ መሆን ያስችላል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት የስማርት ሲቲ ግንባታን ጨምሮ በየደረጃው ዲጂታል አሰራር በመተግበር እየታዩ ያሉ ለውጦች የሚያበረታቱ በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ሲሉም ገልጸዋል።

ስትራቴጂው መረጃዎችን በቀላሉ የመመዝገብ፣ የማስቀመጥና የመለዋወጥ ስራን ቀላልና ፈጣን ማድረጉንም ለአብነት አንስተዋል።

በዋናነት የመንግስት አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ጥራት ያላቸው በማድረግ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025