የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኮሪደር ልማት ስራው የነዋሪው የልማት ተነሳሽነት እንዲጎለብት አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ታኅሣስ 30/2018(ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ ለከተማዋ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር የነዋሪው የልማት ተነሳሽነት እንዲጎለብት አስተዋጽኦ እያበረከተመሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡

የጎንደር ከተማ ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ አካል የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ እና በመጪው የጥምቀት በዓል በይፋ ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር ታውቋል፡፡


የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በከተማዋ የሚከናወነው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ የህዝቡን ተሳትፎ በማቀናጀት የከተማዋን ገጽታ ለመቀየርና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን በሚያሳልጥ መልኩ እየተካሄደ ነው፡፡


የሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማቱ የእግረኞችና የብስክሌት መንገዶችን ጨምሮ ዘመናዊ መናፈሻዎችና ፓርኮችን እንዲሁም አረንጓዴ ስፍራዎችን በማካተት መገንባቱን አስረድተዋል፡፡

የዚሁ ስራ አካል የሆነው የኮንክሪት አስፓልት 8 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር መንገድ ግንባታን በማፋጠን ለጥምቀት በዓል በማጠናቀቅ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡


በተጨማሪም ኮሪደሩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን፣ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራቶችንና ስማርት የመጸዳጃ ቤቶችን ያካተተ ሲሆን ከተማዋ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንድትሆን ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ነው ብለዋል፡፡

የኮሪደር ልማት ስራው ለከተማው ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው በህዝቡ ዘንድም የልማት ተነሳሽነት እንዲጎለብት የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡

ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትርን የሸፈነ ሲሆን በመጪው ጥር ወር በታላቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ስርዓት በሚከበረው የጥምቀት በዓል በይፋ ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር ገልጸዋል፡፡


የከተማውን የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይበልጥ በማነቃቃት በኩል የኮሪደር ልማት ስራው ትልቅ ተስፋን የሰነቀና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውም የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከፍተኛ ወጪ ተደርጎባቸው የተገነቡት ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ለህዝቡ የዘመናት የመልማት ጥያቄ ምላሽ በመስጠት የከተማዋን ዳግም ትንሳኤ ያበሰሩ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች ናቸው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025