የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አዲሱ ቴክኖሎጂ ተቋሙን ወደ ተሟላ የዲጂታል አገልግሎት ስርዓት ያሸጋግራል

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 26/2018 (ኢዜአ)፡-አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ቴክኖሎጂ ተቋሙን ወደ ተሟላ የዲጂታል አገልግሎት ስርዓት የሚያሸጋግር መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የለማውን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓት ዛሬ አስጀምረዋል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በአዲስ አበባ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ስር ነቀል ለውጥ ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ነው፡፡

በተለያዩ ዘርፎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋቱ ነዋሪዎችን ከአላስፈላጊ የገንዘብ እና የጊዜ ብክነት ለመታደግ ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

አገልግሎቱ ይፋ ያደረገው በዲጂታል የታገዘ የአሰራር ስርዓት የተቀናጀ እና የዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችለው አስታወቀዋል፡፡

እንዲሁም ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመዋል፡፡


አዲስ የለማው የዲጂታል ስርዓት የፋይዳ እና የነዋሪነት መታወቂያን በአንድ ላይ አቀናጅቶ የያዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ማንኛውም ግለሰብ በስማርት ስልክ በመታገዝ ከጎግል ፕላይ ስቶር እና ከአፕል ስቶር በማውረድ መጠቀም እንደሚችል ገልጸዋል።

ቴክኖሎጂው ከተቋሙ የሚመነጩ መረጃዎችን በመሰነድ ትክክለኛ ፖሊሲ ለመቅረጽ እና እቅድ ለማዘጋጀት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አስታውቀዋል፡፡

ዲጂታል ስርዓቱ የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እንደሚያሳድገው ጠቅሰው ከሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ50 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ብለዋል፡፡


የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የእድገት ማቀጣጠያ መሳሪያ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ አያሌ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመው፤ በዚህም በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ዘርፎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡


አዲሱ ቴክኖሎጂ የተቋሙን የአገልግሎት ጥራት የሚያሳድግ እንዲሁም ብልሹ የአሰራር ስርዓትን የሚያስወግድ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026