የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢኒሼቲቩ ወጣቶች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያውቁና በዲጂታል ዘርፍ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መሠረት ጥሏል

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡-የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያውቁና በዲጂታል ዘርፍ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መሠረት እንደጣለላቸው ወጣቶች ገለጹ፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ የተደረገው የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች በኦንላይን የኮዲንግ ስልጠና የሚወስዱበት ሂደት ነው፡፡

በኢትዮጵያ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ስታርትአፖች በሀገሪቱ ፈጣን ዕድገት ለማምጣት እና ገበያውን ለመለወጥ የተያዘውን ጥረት በእጅጉ እያገዙ ይገኛሉ፡፡

ይህን ተከትሎ በርካታ ስታርታፖች በቴክኖሎጂ በመታገዝ በሚሰሯቸው ስራዎች የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ የግብርና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የሎጂስቲክስና የኢ-ኮሜርስ ዘርፎች በስፋት ተደራሽ እንዲሆኑ እያስቻሉ ነው፡፡

ኢዜአ ያነጋገራቸው ስታርታፖች ኢኒሼቲቩ የዲጂታል አቅማቸውን በማጎልበት ተጨማሪ ክህሎት እንዲጨብጡ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የአዲስ ኤ አይ ድርጅት መስራች ወጣት ቃልኪዳን ደምሌ፤ በቴክኖሎጂው ዘርፍ በመሰማራት ውጤታማ ስራዎችን ለማበርከት የወሰደችው የኮደርስ ስልጠና በሚገባ እንደጠቀማት ተናግራለች፡፡

በሁለት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የሚሰራ መተግበሪያ በመፍጠር ወደ ስራ ማስገባት መቻሏን የምትናገረው ወጣቷ ለዚህ ስኬትም ስልጠናውን መውሰዷ እንደረዳት ገልጻለች፡፡

ስልጠናው በተለይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳደሪ ለመሆን፣ ፈጠራን ለማላቅ ብሎም የሥራ ዕድሎችን ለማግኘት እንዳስቻላት ጠቅሳለች፡፡

ያሬድ እንዳለ በበኩሉ መንግስት እያደረገላቸው በሚገኘው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ከራሳቸው አልፈው ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግሯል፡፡

የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያውቁና በዲጂታል ዘርፍ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ መሠረት መጣሉን ጠቅሷል፡፡

ይህም ስታርታፖች በቴክኖሎጂው ዘርፍ ራሳቸውንና ሀገራቸውን የሚለውጡ የፈጠራ ስራዎችን እንዲያበረክቱ ዕድል መፍጠሩን ተናግሯል፡፡

የፌዶ ፓወር ሶሉሽን ድርጅት ባለቤት ወጣት ፌደሳ ሹማ በበኩሉ በፈጠራ ውጤቱ በመታገዝ ችግር ፈቺ ስራዎችን በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡

የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስራው ለማሳደግ የሚረዳውን ተጨማሪ ዕውቀት በማስጨበጥ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን እንዳስቻለው ገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026