🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ትብብር ብሩህ እና ይበልጥ ጠንካራ የሚሆንበት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።
ኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ታሪካዊ ወዳጅነትና ትብብር ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል።

የሀገራቱ ግንኙነት በዲፕሎማሲ ትስስርና የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ(ናም) እና የደቡብ ደቡብ ትብብር ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ላይ የተመሰረተ እንደሆነም ተናግረዋል።
ማሌዥያን በጎበኙበት ወቅት የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ላደረጉላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበው ሁለቱ መሪዎች በሀገራቱ የሁለትዮሽ ትብብር ላይ ግልጽ የሆነ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።
ጉብኝቱ ለሀገራቱ ወዳጅነትና ትብብር አዲስ በር የከፈተ መሆኑን ገልጸው በአዲስ አበባ የተደረገው ውይይትም በተለያዩ መስኮች ያለውን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብር ለማጠናከር ዕድል መፍጠሩን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለትዮሽ ውይይቱ ወቅት ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ሊያጎልብቱ በሚችሉባቸው በርካታ ዘርፎች መዳሰሳቸውን ነው ያብራሩት።
የኢትዮጵያ እና ማሌዥያ መጻኢ ጊዜ ብሩህ እና ጠንካራ እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ያሉ ሲሆን ቀሪ ቆይታቸው ፍሬያማ እንዲሆንም ተመኝተውላቸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026