የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ትብብር ብሩህ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ትብብር ብሩህ እና ይበልጥ ጠንካራ የሚሆንበት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ጋር ተወያይተዋል።

ኢትዮጵያ እና ማሌዥያ ታሪካዊ ወዳጅነትና ትብብር ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል።


የሀገራቱ ግንኙነት በዲፕሎማሲ ትስስርና የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ(ናም) እና የደቡብ ደቡብ ትብብር ባላቸው የጋራ ቁርጠኝነት ላይ የተመሰረተ እንደሆነም ተናግረዋል።

ማሌዥያን በጎበኙበት ወቅት የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ላደረጉላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበው ሁለቱ መሪዎች በሀገራቱ የሁለትዮሽ ትብብር ላይ ግልጽ የሆነ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።

ጉብኝቱ ለሀገራቱ ወዳጅነትና ትብብር አዲስ በር የከፈተ መሆኑን ገልጸው በአዲስ አበባ የተደረገው ውይይትም በተለያዩ መስኮች ያለውን የሁለትዮሽና የባለብዙ ወገን ትብብር ለማጠናከር ዕድል መፍጠሩን አንስተዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለትዮሽ ውይይቱ ወቅት ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ሊያጎልብቱ በሚችሉባቸው በርካታ ዘርፎች መዳሰሳቸውን ነው ያብራሩት።

የኢትዮጵያ እና ማሌዥያ መጻኢ ጊዜ ብሩህ እና ጠንካራ እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዳቶ ሰሪ አንዋር ቢን ኢብራሂም ወደ ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ያሉ ሲሆን ቀሪ ቆይታቸው ፍሬያማ እንዲሆንም ተመኝተውላቸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026