የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ እንግልትን በማስቀረት ጊዜና ገንዘባችንን ቆጥቦልናል - ተገልጋዮች

Nov 21, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ህዳር 11/2018(ኢዜአ)፦ የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ እንግልትን በማስቀረት ጊዜና ገንዘባቸውን እንደቆጠበላቸው የከተማዋ ተገልጋዮች ገለጹ።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ህዝቡ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እያነሳቸው የሚገኙ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የተዘረጋ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር ነው።

አገልግሎት አሰጣጡን አስመልክተው ለኢዜአ አስተያየታቸውን ከሰጡ ተገልጋዮች መካከል አቶ ሞአዝ ጅሀድ በማእከሉ የተገኙት የግብር መለያ ቁጥር ለማውጣት መሆኑን ገልፀው በፍጥነት በመስተናገዳቸው ጊዜ ማትረፋቸውን ተናግረዋል።


የተጀመረውን ቀልጣፋ አገልግሎት በማስቀጠል ተገልጋዮች ከአገልግሎቱ ያተረፉትን ጊዜ በልማት ላይ እንዲያውሉት የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ መረጃን በመፈለግ የሚባክንን ጊዜና የተንዛዛ አሰራርን ያሻሻለ መሆኑን የገለፁት ደግሞ ሌላኛዋ ተገልጋይ ወይዘሮ ኢንዲያ መሀመድ አሚን ናቸው።

ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር ረጅም ቀጠሮን ከመስጠት በተጨማሪ አገልግሎቱን በፍጥነት ለማግኘት አዳጋች እንደነበረ አስታውሰው ባገኙት ቀልጣፋ መስተንግዶ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ወይዘሮ ካሚላ ጀማል በበኩላቸው የተጀመረው ዘመናዊና ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥ መጠናከር እንዳለበት ጠቁመው ከመረጃ ዴስክ ሰራተኞች እስከ ባለሙያዎች ያለው ቅንጅታዊ አሰራር የተገልጋዩን እርካታ ማሳደጉን መስክረዋል።


መንጃ ፍቃድ ለማደስ በአገልግሎት ማእከሉ የተገኘው ወጣት አስረስ ዮሀንስ፤ ዘመናዊ አሰራሩ ቀደም ሲል የነበረውን የተዛዛ አገልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የቀየረው በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብሏል።


የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምክትል ስራ አስኪያጅ ጀማል ሳሊ እንዳሉት፤ ዘመናዊ አገልግሎቱ በሰለጠኑ ባለሙያዎችና በቴክኖሎጂ ተደግፎ በተሟላ ሁኔታ እየተሰጠ ነው።

የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ በ25 መስሪያ ቤቶች ከ130 በላይ በሚሆኑ የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶች በቴክኖሎጂ በማስደገፍ እየተሰጠ መሆኑንም አክለዋል።

ይህም ብልሹ አሰራርን በማስቀረትና የተገልጋዩን የአገልግሎት እርካታ በማሳደግ ረገድ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩንም አቶ ጀማል አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026