የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኮርፖሬሽኑ በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ ነው

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 3/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ20 ሺህ ሔክታር ላይ የደረሱ የምርጥ ዘር ሰብሎችን እየሰበሰበ መሆኑን አስታወቀ።

የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽንና ማኅበራዊ ኃላፊነት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ ጋሻው አይችሉህም ለኢዜአ እንዳሉት፥ ተቋሙ በራሱ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻዎች እንዲሁም በኮንትራት ዘር አባዥ እርሻ (በሰፋፊ የባለሃብቶች እርሻ)፣ በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች ማሳ እና በሦስት የግብርና ቴክኒክና ሞያ ትምህርት ሥልጠና ኮሌጆች እርሻ የተባዙ ሰብሎችን እየሰበሰበ ነው።

በአጠቃላይ በ20 ሺህ ሔክታር መሬት ላይ የተባዙ የ22 ሰብሎች 90 ዝርያዎች ምርት እየተሰበሰበ ይገኛል ብለዋል።

ኮርፖሬሽኑ በ2017/18 የምርት ዘመን ለማባዛት ያቀደው 460 ሺህ ኩንታል ዘር መሆኑንም አስታውቀዋል።

በሀገር ደረጃ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማሳካት እየተደረገ በሚገኘው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ ውስጥ ኮርፖሬሽኑ የግብርና ግብዓቶችንና ዘመናዊ የእርሻ መሣሪያዎችን በማቅረብ እንዲሁም የተቀናጀ የሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት ግምባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል ሲሉም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026