የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት የክልሉን ፀጋዎች አልምቶ መጠቀም በሚቻልበት መንገድ ላይ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ ላይ ባቀረቡት የመወያያ ሰነድ በክልሉ የአካባቢውን ፀጋዎችን በማልማት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ገቢዎችን አሟጦ በመሰብሰብ የራስን ወጪ በራስ አቅም በመሸፈን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ማከናወን ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በማልማት የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ከለውጡ ወዲህ በግብርና፣ በማዕድንና ሌሎች ዘርፎች በክልሉ የተገኙ ውጤቶችን በተቀናጀ መልኩ ማስቀጠል ይገባል ያሉት አቶ አሻድሊ፤ በዚህ ረገድ አመራሩ በላቀ ቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በክልሉ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማስፋት፤ ጠንካራ ተቋማት ግንባታ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከልን አጠናክሮ በመቀጠል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026