🔇Unmute
ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በበጀት አመቱ ሶስት ወራት በህገ-ወጥ ንግድ የተሰማሩ ከ49 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ንግድ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ተስፋዬ ገሾ ለኢዜአ እንደተናገሩት በክልሉ ህገ-ወጥ የንግድ ተግባራትን በመከላከል ጤናማ የንግድ ስርዓትን ለማስፈን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው።
በበጀት አመቱ ባለፉት ሶስት ወራት ከክልሉ ፖሊስ፣ ከዐቃቤ ህግ፤ ከገቢዎችና ከትራንስፖርት ቢሮዎች የተውጣጣ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ በየዞኑና በከተሞች ሰፊ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም በተሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ህብረተሰቡ የህገ-ወጥ ንግድ ስራ ላይ የሚያጋጥመውን ወንጀል በማሳወቅና ጥቆማ በመስጠት ከፍተኛ ሚና እንደነበረው ተናግረዋል።
በክልሉ ያለ ንግድ ፈቃድ ንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ፤ ምርትን ከባዕድ ነገሮች ጋር ቀላቅሎ መሸጥ፤ የዋጋ ዝርዝር ያለመለጠፍ የመሳሰሉ ህገወጥ ተግባራት በፈጸሙ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
በተጨማሪም ሚዛን የሚያጭበረብሩ፤ ደረሰኝ የማይሰጡ፤ ያለአግባብ ምርትንና ሸቀጦችን የሚያከማቹ እና የሚደብቁ የንግድ ተቋማት ላይ ማስጠንቀቂያ የመስጠት፣ የማሸግና ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች ተወስዷል ነው ያሉት።
በተለይም በነዳጅ ህገ ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ 30 ግለሰቦች በህግ ተጠያቂ የሆኑ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አምስት ሰዎች በ4 አመት እስር እንዲቀጡ መደረጉን ተናግረዋል።
ቢሮው ህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ አካላትን ወደ ህጋዊ መስመር እንዲመለሱ የማድረጉንና ጤናማ የንግድ ስርዓት ላይ ያሉትን ደግሞ የማበረታታት ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026