የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረበት ጊዜ አብቅቶ አሁን የመብት ጥያቄ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፦ የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረበት ጊዜ አብቅቶ አሁን የመብት ጥያቄ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ምሁራን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ለምክር ቤት አባላት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ህጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ መብት የነበራት ብትሆንም ለምን እና በማን ውሳኔ እንዳጣች እስካሁን መረጃና ማስረጃ ማግኘት አለመቻሉን መግለጻቸው ይታወሳል።

በመሆኑም ከባህር ልትገለልና የባህር በር ልታጣ አይገባም በማለት መንግስት የባህር በር ጉዳይን የህልውና ጉዳይ አድርጎ ጥረቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የታሪክ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ እና በአውስትራሊያ የናሽናል ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዳንኤል መኮንን፤ የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረበት ጊዜ አብቅቶ የመብት ጥያቄ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባህር አካሏ የባህር በር ደግሞ የእድገትና ህልውናዋ መሰረት እንደነበር የሚያስታውሱት ፕሮፌሰር አየለ በክሪ፤ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በመንፈግ የባህር በር ለምን አጣች የሚለው ጉዳይ ዜጎችን እያስቆጨ ያለ መሆኑን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ቀይ ባህር ላይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ መብት ያላት መሆኑን መግለፃቸው ተገቢና ትክክለኛ ነው ብለዋል።

ከዚህ በፊት የባህር በር ጥያቄን ማንሳት እንደ ጥፋት ይቆጠር የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ በቁጭት መንግስት የሀገር የህልውና ጉዳይ አድርጎ መያዙን አድንቀው የኢትዮጵያ ህጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ የባህር በር ባለቤትነት መብቷ ምላሽ ሊያገኝ እንደሚገባ በአጽንኦት ሰጥተዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ ከቀይ ባህር በቅርብ ርቀት ላይ ሆነን በተዘጋ ሀገር ውስጥ መኖር የሌለብን በመሆኑ ሁላችንም ለመብትና ተጠቃሚነታችን በጋራ መቆም አለብን ብለዋል።

በአውስትራሊያ ናሽናል ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዳንኤል መኮንን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ መንግስት የያዘው ጠንካራ አቋም የሚደነቅ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ካላት የህዝብ ቁጥር እና ግዙፍ የኢኮኖሚ ዕድገት አንፃር የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለምክር ቤት አባላት በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑ ማንሳታቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት ምክንያትም በማን እንደተወሰነ የሚያመላክት አንዳችም ማስረጃ እንደሌለ ጨምረው ማስረዳታቸው እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026