የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሁሉም በረከትን ይዞ የመጣ ታላቅ ዕድል ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሁሉም በረከትን ይዞ የመጣ ታላቅ ዕድል ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲፕሎማሲ ጉዳዮችን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ሁሉም ሀገር በተፈጥሮ ጸጋው ሌላውን ሳይጎዳ የመጠቀም መብት አለው ብለዋል፡፡

ሁሉም አገር ሁለት ወሳኝ ጉዳዮች እንዳሉት ገልጸው እነዚህም ብሄራዊ ጥቅምና የብሄራዊ ደህንነት ስጋቶች ናቸው ብለዋል፡፡

እነዚህን ስጋቶች ባለው መረጃ ልክ እንደሚወሰኑ ጠቅሰው፤ ሀገራት በመረጃ እጦት ወይም መሳሳት ብሄራዊ ጥቅምን በተገቢው መንገድ ሊተረጉሙት አይችሉም ብለዋል፡፡

የሰው ልጅ ፍትህን ለማረጋገጥ መትጋት እንዳለበት የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢ-ፍትሃዊ ውሳኔ ባለበት ዓለም ላይ የተሟላ ሰላም ሊፈጠር አይችልም ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በብሄራዊ ጥቅሟ ላይ ኢ-ፍትሃዊ በደል ደርሶባታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ቢያንስ ይህንን መናገር አትከልክሉን ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዓባይ ተጠቀመችበት እንጂ ማንን ጎዳች፣ ኢነርጂ አመረተች እንጂ መች ውሃ ከለከለች፣ እኛ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት መጠቀም እንጂ ማንንም መጉዳት አንፈልግም ብለዋል፡፡

ውሃው ጨመረ እንጂ መች ቀነሰ፣ ሳንጠቀም ድርቅ ነበር ፣አሁን ግድቡን ባንገድበው ኖሮ የጎርፉ ስጋት ምን ያመጣ ነበር ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ግብጻውያንና ሱዳናውያን ወንድሞቻችን ናቸው፣ ረጅም ዘመን ያስቆጠረና በብዙ መልኩ የተጋመድን ህዝቦች በመሆናችን ከኢትዮጵያ ልማት መጠቀም ነው እንጂ ኢትዮጵያ እንዳትለማ መከልከል ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡

ሶስቱ ሀገራት ህዝባቸውን በማስተባበር በጋራ በመስራት ለአፍሪካውያን መትረፍ እንችላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሁሉም በረከትን ይዞ የመጣ ታላቅ ዕድል መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ነገር ግን ማንም ሃይሉን በጉልበት ሊጭንብን አይችልም ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026