🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018(ኢዜአ)፦ ጥራቱን የጠበቀ ቡና በማልማት ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የኦሮሚያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች ገለጹ።
በግብርናው ዘርፍ ለሀገሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ከሚገኙ ምርቶች መካከል ቡና ተጠቃሽ ነው።
ኢትዮጵያም ቡናን ወደ ውጭ በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ አቅም እየፈጠረ እንደሚገኝ ይታወቃል።
የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ እና የቡናና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ሃላፊ መሀመድ ሳኒ በክልሉ ቡናን የማልማት ስራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ቡና ለሀገሪቱ ልማት የሚኖረውን አበርክቶ በአግባቡ ለመጠቀም የቡና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ያረጁ የቡና ተክሎችን በአዲስ በመተካት፣ የቡና አመራረትን የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋል፣ ተመራጭ የሆኑ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ማከፋፈልን ጨምሮ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡናና ሻይ ልማት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ካሳሁን ታዬ፤ በክልሉ በቡና ዘርፍ የሚሰሩ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ ለቡና አመራረት ሂደት ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት ውስጥ ምርት የማይሰጡ የቡና ተክሎችን በሌላ የመተካት፣ ምርጥ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን ከምርምር ተቋማት ጋር ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ የማድረግ ተግባር መጠናከሩን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በስፋት የቡና ችግኞች እንዲፈሉ በማድረግ ለተጠቃሚዎች እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026