የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሎቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡና ብልፅግናን እውን በሚያደርጉ የልማት ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦በክልሎቹ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡና ብልፅግናን እውን በሚያደርጉ የልማት ሥራዎች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የጋምቤላና ሲዳማ ክልሎች ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ገለፁ።

የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ጋትሉዋክ ሮን በክልሉ በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ለሚፈልጉ አካላት በርካታ አማራጮች መኖራቸውን ተናግረዋል።

በማዕድን ዘርፍ የሚታየውን ህገወጥ ተግባር በመቆጣጠርና ፍትሃዊ አሰራር በማስፈን ከክልሉ አልፎ እንደአገር የተሻለ ገቢ ማግኘት እንደሚቻል ገልፀዋል።

በክልሉ ለግብርና ምቹ የሆነ ሰፊ መሬት፣ የቁም እንስሳትና የዓሳ ሀብት በመኖሩ ያለውን ሀብት በመጠቀም፣ የግብይት ስርዓቱን በማሳለጥና የአገር ውስጥና ቀጣናዊ የንግድ ትስስርን በማጠናከር ገቢን ማሻሻል ይቻላል ብለዋል።

በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው በተለይም በሆቴል ልማት፣ መሬት አስተዳደርና ህገ ወጥ ኬላ ላይ የሚታዩ ችግሮችን በመቆጣጠር በክልሉ የሚሰበሰበውን ገቢ ለማሳደግ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ ከተረጂነት ለመውጣት የጀመረችውን ጉዞ ለማሳካት በክልሉ የተጀመረውን ልማት በማጠናከር የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልፀዋል።

የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በየነ በራሳ በበኩላቸው፤ ክልሉ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በትምህርት ለትውልድ መርሃ ግብር በላቀ የህዝብ ተሳትፎ የትምህርት ቤቶች ገፅታ እየተቀየረ መምጣቱን አስታውቀዋል።

በጤና፣በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርና በእርሻ ልማት አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልፀዋል።

በክልሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፥ የግለሰቦችን ህይወት ለመቀየር የቤተሰብ ብልፅግና (አቴቴ ጅሬኛ) የተሰኘ መርሃ ግብር እየተተገበረ መሆኑን በአብነት ጠቅሰዋል።

በዚህም የክልሉን ሀብት በመጠቀም የክልሉን ብሎም የአገርን ብልፅግና እውን ለማድረግና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮቹ በክልላቸው በተያዘው ዓመት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀው፤ ይህንንም ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የገቢ ዘርፍ ሪፎርም የሀገር ብሎም የክልሎች የገቢ አሰባሰብ አፈፃፀም እድገት ለማስመዝገብ ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡

በዘርፉ ያሉ ችግሮችን በቅንጅት በመፍታት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026