የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅንጅት መስራት ይገባል

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልዲያ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት አባላት ገለጹ።

የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር፣ 12ኛ ዓመት፣ 17ኛ አስቸኳይ ጉባዔውን አካሂዷል።

ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አሳዬ በላይነህ እና ደረበ አያሌው፤ በከተማ አስተዳደሩ የተያዙ እቅዶችን በመደገፍና ክትትል በማድረግ ለተፈፃሚነታቸው በትኩረት እንሰራለን ብለዋል።

የወልዲያ ከተማና አካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም በቅንጅት መሰራት እንዳለበት የምክር ቤቱ አባላት አስገንዝበዋል።


የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ፤ በክረምቱ ህብረተሰቡንና አጠቃላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን ያሰተፉ የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

በዚህም መሰረት ከ54ሺህ 300 በላይ ሰዎች የተሳተፉባቸው የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ በትምህርት ቤቶች የቁሳቁስ ማሟላትና ምቹ የማድረግ ስራ፣ የደም ልገሳ እና ሌሎችም አገልገሎቶች ተከናውነዋል ብለዋል።

በክረምቱ የታየው ጥሩ ጅምርና መልካም ተሞክሮን በመቀመር በበጋ ወቅትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026