የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ጥቁር አፈር መሬትን በማንጣፈፍ በምናከናውነው የግብርና ልማት ተጠቃሚ ሆነናል-የደቡብ ወሎ ዞን አርሶ አደሮች

Jul 31, 2025

IDOPRESS

ደሴ ፤ ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦ጥቁር አፈር መሬትን በማንጣፈፍ እና ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በሚያከናውኑት የግብርና ልማት ሥራ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን የደቡብ ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ በዘንድሮ ክረምት ከ96 ሺህ ሄክታር በላይ ጥቁር አፈር መሬትን አጠንፍፎ ለልማት በማዋል ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል።

በዞኑ ጃማ ወረዳ ቀበሌ 06 ነዋሪ አርሶ አደር ኡመር ሁሴን ለኢዜአ እንደገለጹት የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና አዳዲስ አሰራሮችን ተጠቅመው በሚያከናውኑት የግብርና ሥራ ምርታማነታቸው እያደገ መጥቷል።


ውሃ በመቋጠር ከምርት ውጭ የነበረ አንድ ሄክታር የሚጠጋ ጥቁር አፈር መሬታቸውን ዘንድሮ በማንጣፈፍ እና ቴክኖሎጂ ተጠቅመው በስንዴ መዝራታቸውን ገልጸው፣ ከልማቱም ከ40 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የስንዴ ሰብል ቡቃያው ያማረ መሆኑን ጠቁመው፣ ምርታማነታቸውን በማሳደግ ከራስ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተግተው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በግብርና ባለሙያዎች ምክር ጥቁር አፈር መሬታቸውን በማንጣፈፍ ለልማት በማዋል ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ የገለጹት ሌላው የእዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መከተ ከተማው ናቸው።


ዘንድሮም ውሃ የሚቋጥር ግማሽ ሄክታር ጥቁር አፈር ማሳቸውን አጠንፍፈው ስንዴና ጤፍ በመዝራት ተገቢውን እንክብካቤ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

"በመሬቱ ላይ የሚተኛን ውሃ በማንጣፈፍ የተለያየ ሰብል በማልማት ምርታማ መሆን ችለናል" ያሉት ደግሞ የወረኢሉ ወረዳ ቀበሌ 04 ነዋሪ አርሶ አደር ሲሳይ ደምሴ ናቸው።

ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንድ ሄክታር ተኩል መሬታቸውን አጠንፍፈው በመዝራታቸው ቀደም ሲል ከ20 ኩንታል በታች የነበረውን ምርት ወደ 35 ኩንታል ለማሳደግ መቻላቸውን ተናግረዋል።

ያገኙትን ጥቅም ዘላቂ ለማድረግም ዘንድሮ መሬቱን በማጠንፈፍ እና ቴክኖሎጂና አዳዲስ አሰራሮችን በመጠቀም ስንዴና ጤፍ መዝራታቸውን ገልጸዋል።

የጃማ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀይሉ አሰፋ በበኩላቸው በወረዳው በመኸር ከሚለማው 42 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ 32 ሺህ ሄክታር የሚሆነው ጥቁር አፈርን በማንጣፈፍ የሚለማ መሆኑን ተናግረዋል።


አብዛኛው ጥቁር አፈር መሬት በስንዴ እንደሚለማ ጠቁመው፣ ምርታማነትን በአማካይ በሄክታር 46 ኩንታል ማድረስ ተችሏል ብለዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ በበኩላቸው በዞኑ ውሃ የሚቋጥር 96 ሺህ ሄክታር ጥቁር አፈር መሬትን በማንጣፈፍና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በዘር እየተሸፈነ ነው።

"ቀደም ሲል መሬቱ ውሃ ስለሚቋጥር ሰብሉ እየቀጨጨና ቢጫ እየሆነ ተገቢውን ምርት አይሰጥም ነበር" ያሉት ቡድን መሪው አጠንፍፎ የመዝራት ቴክኖሎጂ ከመጣ ወዲህ አርሶ አደሩ ምርታማነትን ማሳደግ ችሏል ብለዋል።

በተጠነፈፈው መሬት ስንዴ፣ ጤፍ፣ ባቄላና ምስር እንደሚለማ ጠቁመው ይህም ምርታማነትን ከእጥፍ በላይ ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን በተያዘው የመኸር ወቅት 432 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ15 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026