የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዓለም አቀፍ አጋሮች ስርዓተ ምግብን ለመደገፍ የገቡትን ቃል ኪዳን በተግባር የመፈጸም ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል-መሐሙድ አሊ ዩሱፍ

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ አጋሮች ስርዓተ ምግብን ለመደገፍ የገቧቸውን ቃሎች በአፋጣኝ ወደ ተግባር እንዲቀይሩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ አሳሰቡ።

ኢትዮጵያ ከጣልያን እና ከተመድ ጋር በመተባበር ያዘጋጀችው ሁለተኛው የምግብ ስርዓት ጉባኤ በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ የምግብ ስርዓት ለውጥ ለማምጣት ጠንካራ የተግባር እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝ ተናግረዋል።


በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካዳፕ)፣ በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና እና ዘላቂ፣ ሁሉን አቀፍ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስርዓት ለመገንባት ስራ 40 ቢሊዮን ዶላር ሀብት የማሰባሰብ ግብ ይዛ እየሰራች መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ዘላቂ፣ እኩልነት የሰፈነበት እና ሁሉን አካታች የምግብ ስርዓትን ለመፍጠር እየተደረገ ያሉ ጥረቶችን የበለጠ ማፋጠን፣ የተገቡ ቃሎችን ወደ ሚለኩ ውጤቶች መቀየር እና የተጠያቂነት ስርዓትን ማስፈን እንደሚገባ አመልክተዋል።

ዓለም አቀፍ አጋሮች የገቧቸውን ቃሎች በተግባር መፈጸም እንዳለባቸው ጠቅሰው የፋይናንስ ተደራሽነት ማሳደግ እና አፍሪካ መር የሆኑ ስራዎችን መደገፍ እንዳለባቸው ተናግረዋል።

የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል፣ የምግብ ዋስትና እና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታን ጨምሮ አፍሪካ ቅድሚያ ከምትሰጣቸው ጉዳዮች ጋር ማጣጣም እንደሚገባቸውም ነው ያሳሰቡት።

ዓለም አቀፍ አጋሮች የገባችሁትን ቃል ኪዳን ወደ ተግባር ቀይሩ ሲሉም ተናግረዋል።

የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽንን ውጤታማ ለማድረግ ጠንካራ አህጉራዊ ትብብር መፍጠር እንደሚገባ ጠቅሰው ሀገራት ስራቸውን ከአፍሪካ ህብረት ማዕቀፎች እና ኢኒሼቲቮች ጋር ማስተሳሰር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም ሀገራቱ በግብርና፣ በስርዓተ ምግብ እና ለአደጋዎች የማይበገር ጠንካራ መሰረተ ልማት መገንባት ስራዎች የሚያፈሱትን መዋዕለ ንዋይ ማሳደግ አለባቸው ነው ያሉት።

በምግብ ስርዓት ፖሊሲ ቀረጻ እና ትግበራ ውስጥ ወጣቶች እና ሴቶችን ዋንኛ ተሳታፊ ማድረግ ወሳኝ መሆኑንም እንዲሁ።

የምግብ ስርዓት ሽግግር ማድረግ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የሞራል ግዴታ እና ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ እንደሆነም አንስተዋል።

የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ረሃብን ለማጥፋት፣ ድህነትን ለመቀነስ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አቅም ግንባታ ቁልፍ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።


#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ


#ኢትዮጵያ


#ምርታማነት

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026