አዲስ አበባ፤ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በማዕድን ዘርፍ ልማት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ለውጥ እያስገኙ መሆናቸውን የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ ገለጹ።
የማዕድን ሚኒስቴር ለማዕድን ዘርፍ የሚውሉ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 29 ተሽከርካሪዎችን እና 81 ላፕቶፖችን ለክልሎች ድጋፍ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ ድጋፍ ያደረገው ለክልሎች፣ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር፣ ለኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት እና ለማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ነው፡፡
የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ንብረቶቹን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው በበጀት ዓመቱ ከማዕድን ዘርፍ የተገኘውን ስኬት መሰረት በማድረግ ውጤቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማስቻል ነው።
ለክልሎች የተደረገው ድጋፍ የማዕድን ዘርፉ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው አብራርተዋል።
ሚኒስቴሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተለያዩ ማዕድናትን ለውጭ ገበያ በመላክ አበረታች ለውጥ ማስመዝገቡን ገልጸዋል ።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ በበኩላቸው፤ የተደረገው ድጋፍ ከዚህ በፊት ያጋጥማቸው የነበረውን የተሸከርካሪ ችግር በማቃለል ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው ነው የገለጹት።
የኦሮሚያ ማዕድን ልማት ባለስልጣን ሃለፊ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ታደሰ ተሾመ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የማዕድን ልማት ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅና ድጋፍ የሚፈልግ ነው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025