
አምቦ፤ ሐምሌ 18/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና በፊት ያለንን የቴክኖሎጂ እውቀት እና ክህሎት ለማዳበር ረድቶናል ሲሉ በምዕራብ ሸዋ ዞን ሰልጣኝ መንግስት ሰራተኞች ገለፁ።
የኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ስልጠና የተከታተሉና ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ሰራተኞች እንዳሉት ስልጠናው ዘመናዊ የዲጂታል መሣሪያዎችን በተግባር ለማዋል በማስቻሉ ክህሎታቸውን በማሳደግ ውጤታማ የሚያደርግ ነው።
ከሰልጣኖች መካከል አቶ ደረጀ ፍቃዱ ፤ ስልጠናውን በመውሰዳቸው በጣም መደሰታቸውን ተናግረው፣ ሰራተኞችና ወጣቶች ችሎታቸውን ለማሳደግና አዳዲስ የስራ እድሎችን ለመፍጠር ስልጠናውን መከታተል እንደሚገባ አንስተዋል።
ሌላው ሰልጣኝ አቶ ራፌራ ደበሳ በበኩላቸው፤ በዚህ በቴክኖሎጂ ዘመን ስልጠናውን መውሰዳቸው እንዳስደሰታቸው ጠቅሰው በዚህም የነበራቸውን ክህሎትና ዕውቀት እንዳዳበረላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወሰደችው ወጣት ገላኔ መልካ በበኩሏ፤ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዲጂታል ዘመኑ ራሷን ብቁ በማድረግ ተወዳዳሪ ለመሆንና የቴክኖሎጂ ክህሎቷን ለማዳበር እንዳስቻላት ተናግራለች።

የምዕራብ ሸዋ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ አዲሷ ሻንቆ፤ በዞኑ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመንግስት ሰራተኞችና ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን ለማዳበር ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
ስልጠናው የቴክኖሎጂ ትስስር በመፍጠርና የወጣቶችን አቅም በማሳደግ እንዲሁም አዳዲስ ስራ ለመፍጠር አይነተኛ ሚና ያለው መሆኑን ጠቅሰው በዞኑ ፍላጎት ያላቸውን የህብረተሰብ አካላት ለማሰልጠን ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

ስልጠናው በቴክኖሎጂ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር አጋዥ በመሆኑ በተለይም ወጣቶች መንግስት ያመቻቸውን እድል በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
በምዕራብ ሸዋ ዞን በ2017 በጀት ዓመት 29 ሺህ የመንግስት ሰራተኞችና ወጣቶች ስልጠናውን በበየነመረብ በመሰልጠን የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ተናግረዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026