አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 162 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
ገቢው የተገኘው ከድምጽ ጥሪ፣ ከኢንተርኔት አገልግሎት፣ ከቫስ፣ ከመሠረተ ልማት ማጋራት፣ ከቴሌኮም ቁሳቁስ ሽያጭና ከሌሎች ምንጮች መሆኑንም ገልጿል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፥ የኩባንያውን የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና መሪ የሶስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ ማጠቃለያ ሪፖርት ለመገናኛ ብዙኃን ይፋ አድርገዋል።
ኢትዮ ቴሌኮም ከሶስት ዓመት በፊት የቴሌኮም እና የዲጂታል አገልግሎትን ማሳደግ የሚያስችል መሪ የሶስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ አዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል።
ኩባንያው ከቴሌኮም አገልግሎት ባሻገር በዲጂታላይዜሽን በኩል አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን አመላክተዋል።
የቴሌኮም አገልግሎት አሰጣጡን ከማስፋትና ጥራቱን ከማሳደግ አኳያ ከፍተኛ እድገት መመዝገቡንም ነው ዋና ስራ አስፈጻሚዋ የገለጹት።
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም ትርጉም ያለው ስራ መሠራቱን አንስተዋል።
በመሪ የሶስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂ ደግሞ 26 ከተሞችን በ5ጂ ኔት ወርክ እንዲሁም 936 ከተሞችን በ4ጂ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።
በዚህም በመላ ሀገሪቱ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን የፈጣን ኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር መፈጠሩን ተናግረዋል።
በ2017 በጀት ዓመት 1ሺህ 683 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች መገንባታቸውንም ነው የጠቀሱት።
በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ10ሺህ በላይ የሞባይል ጣቢያዎች ተተክለው አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙም አመላክተዋል።
በበጀት ዓመቱ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፥ 162 ቢሊዮን ብር ገቢ መገኘቱን አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025