የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የዲላ- ቡሌ- ሐሮ- ዋጮ የአስፋልት መንገድ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ እየተደረገ ያለው ጥረት ሊጠናከር ይገባል

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ዲላ ፤ ሐምሌ 16/2017(ኢዜአ)፦የዲላ- ቡሌ- ሐሮ- ዋጮ የ68 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታን ለማጠናቀቅ የሚደረገው ጥረት መጠናከር እንዳለበት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ።

የጌዴኦ ዞንን የወከሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የዲላ-ቡሌ-ሐሮ-ዋጮ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የስራ እንቅስቃሴን ምልከታ አድርገዋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ስብሳቢ ኢንጂነር ስለሺ ኮሬ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት የአስፋልት መንገድ ግንባታው መጠናቀቅ ለአካባቢው ሁለንተናዊ ለውጥ ድርሻው የጎላ ነው ።

በምልከታቸው የግንባታው ሂደት በጥራት እየተከናወነ ቢሆንም በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ይበልጥ መሰራት አለበት ብለዋል።

ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ በሚደረገው ጥረትም የአካባቢው ህብረተሰብ የሚያደርገውን ድጋፍ ማጠናከር እንዳለበትም ተናግረዋል።


የመንገዱን ግንባታ በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ውል ታስሮ በ2015 ዓ/ም ወደ ስራ መገባቱን ያነሱት ደግሞ የግንባታ ፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ኃላፊ ኢንጂነር ሉላዊ አያሌው ናቸው።

ይሁንና ባለፉት ሁለት ዓመታት የግንባታ ፕሮጀክቱ ከሚሸፍነው 68 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር ውስጥ 6 ኪሎ ሜትር ብቻ መሰራቱን አንስተው ለዚህም የወሰን ማስከበር ስራው ችግር ሆኖ መቆየቱን ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን የአካባቢው አስተዳደርና የክልሉ መንግስት በቅንጅት ችግሩን ፈተው የግንባታ ሂደቱ እየተፋጠነ እንደሚገኝም አንስተዋል።


በተለይ የአፈር ስራ፣ የግብዓት ዝግጅትና የፍሳሽ መውረጃ ቦዮች ስራ እየተፋጠነ መሆኑን አንስተው የአስፋልት ማልበሱን ስራ በአጭር ጊዜ በመጀመር ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የጌዴኦ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስለሺ ሽፈራው በበኩላቸው መንገዱ የዲላንና የቡሌ ወረዳዎች እንዲሁም በምስራቅ ጉጂ ዞን በኩል ዳማና ኡራጋ ወረዳዎችን የሚያስተሳስር መሆኑን አስረድተዋል።

ይህም የግብርና ምርቶችን ወደ ገበያ ለማውጣት በማገዙ ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አመልክተዋል።

ለዚህም የመንገዱን ግንባታ ለማፋጠን የዞኑ አስተዳደር የግንባታ ግብዓት ማምረቻ ቦታ ከይገባኛል ነጻ በማድረግ ለአስፋልት ስራው መፋጠን የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝም ነው ያነሱት።


በጌዴኦ ዞን የቡሌ ከተማ ነዋሪ አቶ አብርሃም ሃይሉ በበኩላቸው ቀደም ሲል በአካባቢያቸው የመንገድ መሰረተ ልማት እጥረት በመኖሩ የአካባቢው ልማት እንዲጓተት ምክንያት ሆኖ መቆየቱን ጠቁመዋል።

አሁን ላይ የአስፓልት መንገዱ ግንባታ በመጀመሩ ይዞታቸውን በወቅቱ በማንሳት ለስኬቱ የድርሻቸውን መወጣታቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026