
ደብረ ብርሃን፤ ሐምሌ 14/2017(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 25 ኢንዱስትሪዎች ወደማምረት መሸጋገራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው የ2017 ዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸምን የሚገመግምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ላይ ያተኮረ መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።
የከተማ አስተዳደሩ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ሃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት በከተማው የሚከናወኑ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ሥራዎች ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ሚና አላቸው።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዘርፉን ለማጠናከር በተደረገ ጥረት በከተማው 25 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 232 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው፣ ባለሀብቶቹ ወደሥራ ሲገቡ ከ21 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል ይፈጥራሉ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን መሰረት በማድረግ በተካሄደ ጥረትም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከውጭ የሚገባን ተኪ ምርትና ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከልም አቶ አየለ ደስታ እንደገለጹት በአካባቢው በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፍ የታየው መነቃቃት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ ጽጌ ዋሪ በበኩላቸው በአካባቢው ያለውን ጸጋ ለማስተዋወቅ የተሰራው ሥራ የባለሀብቶች ፍሰት እንዲጨምር ማስቻሉን ተናግረዋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ በበጀት ዓመቱ በኢንቨስትመንት ዘርፍ በአጠቃላይ ለ5 ሺህ 113 ሰዎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ከመምሪያው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026