
አሶሳ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
በክልሉ በመኸር እርሻ ከሚለማው መሬት ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተመላክቷል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ አቡራሞ ወረዳ አንጉላሎ ቀበሌ ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በኩታ-ገጠም እየለማ ያለ የበቆሎ ማሳን ዛሬ ተመልክተዋል።

አቶ አሻድሊ በዚህ ወቅት እንደገለጹት አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የግብርና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
የአርሶ አደሩ በኩታ ገጠም የማልማት ልምዱ እያደገ መሆኑን ጠቁመው፣ በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እስካሁንም ከ1 ሚሊዮን 500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አቶ አሻድሊ ጠቁመው፣ ከመኸር እርሻ ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።

የዘንድሮው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወረዳው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ከመመልከት ጎን ለጎን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026