የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሐምሌ 13/2017(ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

በክልሉ በመኸር እርሻ ከሚለማው መሬት ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተመላክቷል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ አቡራሞ ወረዳ አንጉላሎ ቀበሌ ከ3 ሺህ 200 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በኩታ-ገጠም እየለማ ያለ የበቆሎ ማሳን ዛሬ ተመልክተዋል።


አቶ አሻድሊ በዚህ ወቅት እንደገለጹት አርሶ አደሩ ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የግብርና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

የአርሶ አደሩ በኩታ ገጠም የማልማት ልምዱ እያደገ መሆኑን ጠቁመው፣ በተያዘው የመኸር ወቅት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁንም ከ1 ሚሊዮን 500 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አቶ አሻድሊ ጠቁመው፣ ከመኸር እርሻ ከ55 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል።


የዘንድሮው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወረዳው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴን ከመመልከት ጎን ለጎን ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026