አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017 (ኢዜአ):-በከተማ አስተዳደሩ የሚዘጋጁ ኤግዚቢሽን እና ባዛር የአምራች እና የሸማቹን የገበያ ትስስር እያጠናከሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ ገለጹ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ያዘጋጀውና ከሃምሌ 7 እስከ ሃምሌ 11/2017 ዓ/ም በኤግዚቢሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው እለት ተጠናቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቢሮው የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ከዚህ ውስጥ የንግድ ስርአቱን ቀልጣፋ እንዲሆን አምራች እና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት በኩል ውጤታማ ስራ መሰራቱን ለአብነት አንስተዋል፡፡
2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛርም የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
ለ5 ቀናት በቆየው ኤግዚቢሽን እና ባዛር የአገር ውስጥ ምርቶችና አገልግሎቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለህብረተሰቡ ትልቅ ፋይዳ ማስገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡
በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት መፈጸማቸውን አንስተው ከ43 ሚሊየን ብር በላይ ግብይት መከናወኑንም አስታውቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፍስሃ ጥበቡ በበኩላቸው፤ ባዛሩ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ትስስር የተፈጠረበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ቢሮው አቅራቢዎችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገበያዩበት ምቹ ሁኔታን የመፍጠር ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
ከሸማቾች መካከል አልማዝ አበበ እንደገለጸችው ከባዛሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን በመግዛት ተጠቃሚ መሆኗን ተናግራለች፡፡
ምርታቸውን በባዛሩ ያቀረቡት አቶ ደረጀ ጋሪ በበኩላቸው፤ ባዛሩ መዘጋጀቱ ምርቶቻቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ እንዲያቀርቡ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025