
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017 (ኢዜአ):-በከተማ አስተዳደሩ የሚዘጋጁ ኤግዚቢሽን እና ባዛር የአምራች እና የሸማቹን የገበያ ትስስር እያጠናከሩ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ ገለጹ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ያዘጋጀውና ከሃምሌ 7 እስከ ሃምሌ 11/2017 ዓ/ም በኤግዚቢሽን ማዕከል ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው እለት ተጠናቋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሃቢባ ሲራጅ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ቢሮው የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ከዚህ ውስጥ የንግድ ስርአቱን ቀልጣፋ እንዲሆን አምራች እና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት በኩል ውጤታማ ስራ መሰራቱን ለአብነት አንስተዋል፡፡
2ኛው ከተማ አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛርም የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
ለ5 ቀናት በቆየው ኤግዚቢሽን እና ባዛር የአገር ውስጥ ምርቶችና አገልግሎቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለህብረተሰቡ ትልቅ ፋይዳ ማስገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡
በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት መፈጸማቸውን አንስተው ከ43 ሚሊየን ብር በላይ ግብይት መከናወኑንም አስታውቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፍስሃ ጥበቡ በበኩላቸው፤ ባዛሩ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ትስስር የተፈጠረበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡

ቢሮው አቅራቢዎችና ሸማቾች በቀጥታ የሚገበያዩበት ምቹ ሁኔታን የመፍጠር ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡
ከሸማቾች መካከል አልማዝ አበበ እንደገለጸችው ከባዛሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን በመግዛት ተጠቃሚ መሆኗን ተናግራለች፡፡

ምርታቸውን በባዛሩ ያቀረቡት አቶ ደረጀ ጋሪ በበኩላቸው፤ ባዛሩ መዘጋጀቱ ምርቶቻቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ እንዲያቀርቡ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026