
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ "ዙሪያ" የተሰኘው መተግበሪያ የንግድ ስርዓቱን በማቀላጠፍ፣ የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ በመቆጠብ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና ገለጹ።
ኢትዮ ቴሌኮም፣ ዳሽን ባንክ እና ኢታ ሶሊዩሽን የንግድ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን የሚያቀላጥፍ "ዙሪያ" የተሰኘ የቢዝነስ አውቶሜሽን ሶሉሽን መተግበሪያ ይፋ አድርገዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ችፍ ሞባይል መኒ ቢዝነስ ኦፊሰር ብሩክ አድሃና እንዳሉት፣ መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱን በማዘመን የተገልጋዮችን ጊዜና ገንዘብ የሚቆጥብ ነው።
የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በቀላሉ ለማወቅ እንደሚረዳና ለነጋዴዎች የተሻለ የክፍያ መፈጸሚያ አማራጭ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
"ዙሪያ" ለአጠቃቃቀም ቀላል እና ፈጣን፣ ደህነንቱ የተረጋገጠ መሆኑንም ጨምረው አንስተዋል።
የውጪ እና የሀገር ውስጥ የክፍያ ካርዶችን እንደሚቀበልና የሂሳብ ስራን ቀላል እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።
በወረቀትና በማሽን ይሰራ የነበረውን የክፍያ ስርዓት ወደ አንድ ወጥ አተገባበር የሚያመጣ መተግበሪያ እንደሆነም ጠቁመዋል።
መተግበሪያው የንግድ ስርዓቱንና አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026