የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ ከእጣንና ሙጫ ሽያጭ ከ108 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ

Jul 11, 2025

IDOPRESS

ገንዳ ውሃ ፤ሃምሌ 3/2017 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ጎንደር ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከእጣንና ሙጫ ሽያጭ ከ108 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የምዕራብ ጎንደር ዞን የአካባቢና ደን ጥበቃ ተጠሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በጽህፈት ቤቱ የአካባቢ የህግ ተከባሪነትና የማህበረሰብ ተፅዕኖ ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ሀብታሙ አድጎ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ ከፍተኛ የሆነ የእጣንና የሙጫ ደን ሀብት አለ።

በዞኑ ከሚገኘው 760 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ በደን የተሸፈነ መሬት ከ234 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በእጣንና ሙጫ ዛፍ የተሸፈነ መሆኑን ገልጸዋል።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ17 ማህበራትና ባለሃብቶች 5 ሺህ 80 ኩንታል ምርት በመሰብሰብና ለገበያ በማቅረብ ከ108 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል።

አምራቾች ካገኙት ገቢ በተጨማሪ በሮያሊቲ ታክስ ክፍያ ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገኘታቸውን አስረድተዋል።

በዘርፉ ለ722 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል የተፈጠረላቸው መሆኑን ጠቁመው ይህም ዘርፉ ከገቢ ባሻገር ዋና የስራ እድል መፍጠሪያ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ገልፀዋል።

በዞኑ በመተማ፣ በቋራና በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳዎች የተመረተው የእጣንና ሙጫ ምርት በላኪዎች በኩል ወደ ውጭ ተልኮ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመተማ ወረዳ ሌንጫ ቀበሌ አዲስ ህይወት የህብረት ስራ ማህበር ሰብሳቢ የሆኑት አቶ በየነ ውቤ እንዳሉት ማህበሩ 60 አባላቱን በማሳተፍ በበጀት ዓመቱ 229 ኩንታል እጣንና ሙጫ ማምረት ችሏል።

ያመረቱትን እጣንና ሙጫ አንዱን ኩንታል በ53 ሺህ ብር በጨረታ በመሸጥ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።


የእጣን ዛፉ ዘላቂ ጥቅም እንዲሰጥም ባገኙት ስልጠናና ግንዛቤ ፈጠራ በመመስረት በማምረት ሂደትና ከምርት በኋላ ተገቢውን እንክብካቤ እያደረጉ መሆኑንም አስረድተዋል።

በዚሁ ወረዳ የላይኛው ለምለም ተራራ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ማህበር አባል አቶ ሙሀመድ አደም በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ 109 ኩንታል ምርት በመሰብሰብ ለገበያ አቅርበው በመሸጥ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ማህበራቸው 190 አባላት ያለው ሲሆን በቀጣይ የተሻለ ምርት ለማምረት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

የእጣንና ሙጫ ደንን ለማስፋፋት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑም ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026