የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ሰመራ ፤ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)፡- በአፋር ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ አወል አብዱ የበጀት ዓመቱን የገቢ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸው፤ በዚህም ከዕቅድ በላይ 6 ቢሊዮን 40 ሚሊዮን 398 ሺህ 943 ብር መሠብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር 46 በመቶ ልዩነት ያለውና 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።

ገቢው የተሰበሰበው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆነ ታክሰና ታክሰ ካልሆኑ የገቢ አርዕሰት መሆኑንም ኃላፊው ተናግረዋል።

ለበጀት ዓመቱ ከዕቅድ በላይ ክንውን ተከታታይነት ያለውና በየደረጃው ያሉ የአመራርና የዘርፉ ባለሙያዎች ቁርጠኝነት የታከለበት ስራ በመከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።

በበጀት ዓመቱ ደረሰኝ ካለመቁረጥ ጀምሮ በህገ ወጥነት የተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ የእርምት እርምጃ መወሰዱንም አቶ አወል አስታውቀዋል።

አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የስነ-ምግባር ጥሰቶችን በማረም ህገ ወጥነትን ወደ ህግ የመመለስ ስራዎች መከናወኑንም አክለዋል።

ክልሉ ካለው እምቅ አቅም ጋር የተመጣጠነ ገቢ ለመሰብሰብ በቀጣዩ ዓመት ትኩረት የተሰጠ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026