አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማን የመንገድ መሰረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ ለማሳደግ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞችና በየደረጃው የሚገኘው አመራር የበለጠ መትጋት እንዳለባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት በመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታው መስክ ለተገኘው ስኬት ለሰራተኞቹ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር አካሂዷል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ከንቲባዋ እንደገለጹት የከተማዋ የመንገድ ሽፋን ገና ብዙ መስራትን የሚጠይቅ ነው።
በዚህ ሒደት የባለስልጣኑ ሰራተኞች አሁን ለተደረሰበት ደረጃ ያሳዩት ትጋትና የስራ ተነሳሽነት የሚያስመሰግናቸው እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።
ከተማችን አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እስከምትሆን ድረስ 24/7 ነው የምንሰራው ያሉት ከንቲባዋ ለሰራተኞቹ የተሰጠው እውቅና እና ምስጋና የበለጠ ሞራል ሆኖ የተሻለ ለመፈጸም እንደሚያነሳሳ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሰራተኞቹ እስከዛሬ ያሳዩትን ትጋት የበለጠ በማጠናከር ለከተማዋ የመንገድ ሽፋን እድገት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በበጀት አመቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ብዙ ቅሬታ የነበረባቸውን ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን ያስታወሱት ደግሞ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሙህዲን ረሻድ ናቸው።
አሁን ለተገኘው ውጤትም በትጋት የሰሩት የባለስልጣኑ ሰራተኞችና አመራሮች ምስጋና እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ የህዝብ የመልካም አስተዳደር ቅሬታ ሲነሳባቸው የነበሩትን ጨምሮ 31 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ርዝመት ያላቸው 13 የመንገድ ፕሮጀክቶች እና 8 ድልድዮች ተጠናቀው ለምረቃ እንዲበቁ ማድረጉ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025