የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የከተማዋን የመንገድ መሰረተ ልማት ደረጃ ለማሳደግ የበለጠ ተግቶ መስራት ይገባል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማን የመንገድ መሰረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ ለማሳደግ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሰራተኞችና በየደረጃው የሚገኘው አመራር የበለጠ መትጋት እንዳለባቸው ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት በመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታው መስክ ለተገኘው ስኬት ለሰራተኞቹ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር አካሂዷል፡፡

በመርሃ-ግብሩ ላይ ከንቲባዋ እንደገለጹት የከተማዋ የመንገድ ሽፋን ገና ብዙ መስራትን የሚጠይቅ ነው።


በዚህ ሒደት የባለስልጣኑ ሰራተኞች አሁን ለተደረሰበት ደረጃ ያሳዩት ትጋትና የስራ ተነሳሽነት የሚያስመሰግናቸው እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።

ከተማችን አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እስከምትሆን ድረስ 24/7 ነው የምንሰራው ያሉት ከንቲባዋ ለሰራተኞቹ የተሰጠው እውቅና እና ምስጋና የበለጠ ሞራል ሆኖ የተሻለ ለመፈጸም እንደሚያነሳሳ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ሰራተኞቹ እስከዛሬ ያሳዩትን ትጋት የበለጠ በማጠናከር ለከተማዋ የመንገድ ሽፋን እድገት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በበጀት አመቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ብዙ ቅሬታ የነበረባቸውን ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን ያስታወሱት ደግሞ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሙህዲን ረሻድ ናቸው።

አሁን ለተገኘው ውጤትም በትጋት የሰሩት የባለስልጣኑ ሰራተኞችና አመራሮች ምስጋና እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ የህዝብ የመልካም አስተዳደር ቅሬታ ሲነሳባቸው የነበሩትን ጨምሮ 31 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ርዝመት ያላቸው 13 የመንገድ ፕሮጀክቶች እና 8 ድልድዮች ተጠናቀው ለምረቃ እንዲበቁ ማድረጉ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026