የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ፎረሙ ምርቶቻችንን ያስተዋወቅንበትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ ልምድ ያገኘንበት ነው - አምራቾች

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ ሶስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ የሚያስችል ልምድ እንዲያገኙ ማስቻሉን በፎረሙ በተከፈተው ኤግዚቢሽን የተሳተፉ አምራቾች ገለፁ።

ላለፉት ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ዛሬ ተጠናቋል።

የማጠቃለያ መርሃ ግብሩም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ሚኒስትሮች፣ ሥራ ፈጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል።

በፎረሙ ላይ ምርቶቻቸውን ይዘው የቀረቡ በማምርቻው ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች እንዳሉት ፎረሙ የገበያ ትስስር የፈጠሩበትና የተሻለ ልምድ ያገኙበት ነው።

ከአምራቾቹ መካከል የቆዳ ውጤቶች ማምረት ሥራ ላይ የተሰማሩት ሶስና ሲሳይ፥ ከዚህ ቀደም የቆዳ ውጤቶችን ገዝተው ሲሸጡ መቆያተቸውን አውስተዋል።

ከሁለት ዓመት ወዲህ የቆዳ ምርቶችን በእጅ በመስራት ወደ ገበያ ማቅረብ የጀመሩ ሲሆን ከራሳቸው አልፎ ለስድስት ሰዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ገልፀዋል።

ፎረሙ በዘርፉ የተሻለና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉበት ልምድ ማግኘታቸን ነው ያስረዱት።

ለሁለት አስርት ዓመታት የሚጠጋ ጊዜ ተቀጥረው ሲሰሩ የቆዩት ጌጤ አስፋው በበኩላቸው ለወትሮው ለራሳቸውና ለሚቀርቧቸው ሰዎች የሹራብ አልባሳትን በስጦታ መልክ ሰርተው ያቀርቡ እንደነበር ተናግረዋል።

አሁን ላይ ሶስት ሆነው በመደራጀት የጀመሩት ቢሊሌ የሹራብ አልባሳት ስራ አድጎ፥ ለአራት ሰዎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠሩን ጠቁመዋል።

የአፍሪካ ሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም የገበያ ትስስር ከመፍጠር ባለፈ ልምድ እንዲለዋወጡና የላቀ መነሳሳትን እንዲፈጥሩ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።

ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ባህላዊ አልባሳትን መስራት የጀመሩት የዕለት ገብረአብ፥ አሁን ላይ 5 የቤተሰብ አባላትን በሙያ አሰልጥነው ወደ ስራ ማስገባታቸውን ነው ያነሱት።

የተለያዩ አልባሳትና የደንብ ልብሶችን ላለፉት 9 ዓመታት በማምረት ለገበያ ሲያቀርብ የቆየው የሎዛ ጋርመንት ምክትል ስራ አስኪያጅ ገነት ጥላሁን በበኩላቸው፥ አሁን ላይ ከ20 በላይ ለሆኑ ሰዎች ቋሚ የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል።

ፎረሙ ምርቶቻቸውን የተሻለ ማድረግ የሚችሉበት ተሞክሮ ያገኙበትና የሀገር ውስጥ ምርትን ለማበረታታት አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል።

አምራቾቹ በተለይም ወጣቶች ከጠባቂነት ይልቅ ስራ ፈጣሪ ለመሆን ፍላጎታቸውን መሰረት ያደረገ ስራ ላይ አተኩረው እንዲሰሩም መክረዋል።

አሁን ላይ ያለውን ሰፊ የስራ እድል በመጠቀም ስራ ፈጣሪ በመሆን ራን፣ ቤተሰብን እና ሀገርን ለመጥቀም ተግቶ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026