
ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ቦረና ዞን ከ4 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ዛሬ በነገሌ ቦረና ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፡፡

በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን እንደገለጹት፤ ለአገልግሎት ከበቁት ውስጥ የመጠጥ ውሀ፣ የጤና፣ የትምህርትና የመንገድ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።
የመንግስት ድጋፍና የሕዝቡ ተሳትፎን ጨምሮ የተገነቡት እነዚህ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባቸው አስታውቀዋል።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው የሕብረተሰቡን የመሰረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡
ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ መሳካት ሕዝቡ ፣ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ፤ የክልሉ መንግስት የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እንዳስገነባ ገልጸዋል፡፡
በምስራቅ ቦረና ዞን የተገነቡት ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶች የግንባታ አፈጻጸም ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል፡፡
መንግስት የአርብቶ አደሩን ፍትሀዊ የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የጀመረው ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
የዞኑ ሕዝብ የአካባቢውን ሰላምንና የተገነቡ ፕሮጀክቶች በመጠበቅና በመንከባከብ የድርሻውን እንዲወጣም መልዕከት አስተላልፈዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026