የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምስራቅ ቦረና ዞን ከ4 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት በቁ

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ)፡- በምስራቅ ቦረና ዞን ከ4 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ዛሬ በነገሌ ቦረና ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መርቀዋል፡፡


በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን እንደገለጹት፤ ለአገልግሎት ከበቁት ውስጥ የመጠጥ ውሀ፣ የጤና፣ የትምህርትና የመንገድ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ይገኙበታል።

የመንግስት ድጋፍና የሕዝቡ ተሳትፎን ጨምሮ የተገነቡት እነዚህ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባቸው አስታውቀዋል።

ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው የሕብረተሰቡን የመሰረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ደረጃ በደረጃ ምላሽ ለመስጠት የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡

ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ መሳካት ሕዝቡ ፣ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ምስጋና አቅርበዋል፡፡


በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ሳዳት ነሻ ፤ የክልሉ መንግስት የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ከ200 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች እንዳስገነባ ገልጸዋል፡፡

በምስራቅ ቦረና ዞን የተገነቡት ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶች የግንባታ አፈጻጸም ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ብለዋል፡፡

መንግስት የአርብቶ አደሩን ፍትሀዊ የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የጀመረው ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

የዞኑ ሕዝብ የአካባቢውን ሰላምንና የተገነቡ ፕሮጀክቶች በመጠበቅና በመንከባከብ የድርሻውን እንዲወጣም መልዕከት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025