አሶሳ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ የተገነባልን የመስኖ መሰረተ ልማት ልማቱን በስፋት ለማከናወን ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኡራ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ በ74 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ የፀንፀሀሎ የመስኖ መሠረተ ልማት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን በተገኙበት ተመርቋል።
የመስኖ ፕሮጀክቱ 200 ሄክታር ማሳ ማልማት የሚችልና ከ800 በላይ የሚሆኑ የሶስት ቀበሌ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች የመስኖ መሠረተ ልማቱ ከዚህ በፊት የሚያከናውኑትን የመስኖ ልማት ለማስፋፋት እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል።
አርሶ አደር ሙሀመድ ሙዘሚል እና ዳውድ አጣሂር ከዚህ በፊት በአነስተኛ የመስኖ ስራ ሲጠቀሙ ቢቆዩም ብዙም ውጤታማ እንዳልነበሩ ገልፀዋል።
አሁን ላይ የተጠናቀቀው የመስኖ መሰረተ ልማት ከፍተኛ ርዝመት ያለው የውሀ መውረጃ ቦይ ያለውና ውሀን በሁሉም አቅጣጫ ተደራሽ ማድረግ የሚችል በመሆኑ የመስኖ ልማቱን በስፋት ማከናወን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
ሌላው ወጣት አርሶ አደር አብዱ አልቃዲ በበኩሉ የመስኖ መሰረተ ልማት ግንባታው ከመደበኛ የግብርና ስራችን በተጨማሪ በመስኖ ልማት እንድንሳተፍ እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው ብሏል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ባበክር ሀሊፋ በበኩላቸው በክልሉ በዘንድሮው በጀት ዓመት የ11 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቁን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩ በመስኖ ልማት ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸው የመስኖ መሰረተ ልማቱን በመጠቀም የበለጠ ምርታማ መሆን እንደሚቻል ተናግረዋል።
የፀንፀሀሎ መስኖ መሰረተ ልማት ሰፊ የማልማት አቅም ያለው በመሆኑ አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም የተለያዩ የሰብል አይነቶችን በማምረት ተጠቃሚ እንደሚሆን አስታውቀዋል።
የመስኖ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ማህበረሰብ ተሳትፎ የላቀ እንደነበር የገለጹት ደግሞ ግንባታውን ያከናወነው ወርቅነህ ግዛው የውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ስራ አስኪያጅ ወርቅነህ ግዛው ናቸው።
የመስኖ ፕሮጀክቱ ለአሳ እርባታና ለሌሎች የግብርና ስራዎች ምቹ መሆኑ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025