የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ከተረጂነት ለመላቀቅ የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራትን ለማስቀጠል በትጋት ይሰራል

Jul 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ከተረጂነት ለመላቀቅ የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራትን ለማስቀጠል በትጋት እንደሚሰራ የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ባለፉት አምስት ቀናት በደቡብ ኦሮሚያ በሚገኙ አምስት ዞኖች ያደረጉት ጉብኝት ስኬታማ መሆኑ ተገልጿል።


የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ ሀይሉ አዱኛ ጉብኝቱን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ጉብኝቱ የልማት ስራዎችን ውጤታማነት ያረጋገጠ ብሎም የቀበሌ አደረጃጀቶች ለህዝቡ እየሰጡ የሚገኙትን የአገልግሎቶች አሰጣጥ የቃኘ መሆኑንና የታለመለትን ግብ ያሳካ ነው ብለዋል።

በክልሉ ፕሬዚዳንት የተመራ ቡድን በቦረና፣ በምዕራብ ጉጂ፣ በምስራቅ ቦረና፣ በጉጂ እና በባሌ ዞኖች የመስክ ምልከታ ማድረጉን ገልጸዋል።

በዚህም ከተረጂነት ለመላቀቅ ምርታማነትን ለማሳደግ የተያዙ ግቦችን አፈጻጸም በመመልከት ውጤታማ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ የተሰጠበት መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም በቦረና፣ በምዕራብ ጉጂ፣ በምስራቅ ቦረና እና በጉጂ ቆላማ አካባቢዎች ለዘመናት ያልለሙ መሬቶችን በማልማት ለውጥ መምጣት መጀመሩን ገልጸዋል።

በዚህም የስንዴ ምርትን ጨምሮ ሌሎች የሰብል ዓይነቶችን በክላስተር በማምረት ከተረጂነት ለመላቀቅ የተጀመሩ ስራዎችን ውጤታማነት በማረጋገጥ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ ለቀጣይነቱም በትጋት ይሰራል ብለዋል።


ለዚህም በክልሉ መንግስት እየተገነቡ የሚገኙ የፊና የመስኖ ግድብ ፕሮጀክቶች አጋዥ መሆናቸውን በማከል።

በሌላ መልኩ በክልሉ መንግስት ተደራጅቶ ወደ ስራ የገባው የቀበሌ አደረጃጀት ለሕዝቡ በቅርበት አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ የተረጋገጠበት ጉብኝት ነው ብለዋል።

በዚህም አደረጃጀቱ የሕዝቡን የመልካም አስተዳደር እና የልማት ጥያቄዎች በመፍታት ላይ እንደሚገኝ ታይቷል ብለዋል።

በአጠቃላይ ፕሬዚዳንቱ እና የስራ ሃላፊዎች ያደረጉት ጉብኝት ውጤታማ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025